Mols.gov.et

mols mols

News

ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ወደ ሥራ

ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ወደ ሥራ የማስገባት ተግባር በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ
‹‹አካታችነት›› በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ የዋለው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ አንዱ የትኩረት አቅጣጫ ነው፡፡
በዚሁ መሰረት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ ስልጠናዎች ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ወጣቶችን ስደተኞችንና ሌሎችም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን በእኩል ተደራሽ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ይጠበቃል፡፡
የትኩረት አቅጣጫውን ወደ ተግባር ለመለወጥ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ከስደት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በሥደተኞች ላይ በሚሠሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተጎብኝተዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ ወጣቶችንና ተመላሾችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማሰልጠን ወደ ሥራ እንዲገቡ እያደረገ ይገኛል።
ስልጠናው ወጣቶች በቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ እንዲሰማሩና የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱ የሚያስችል ሲሆን ይህም ከጥገኝነት መንፈስ ተላቀው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እድል የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ ስደትን በዘላቂነት ለመከላከል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተገልጿል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወነ ያለው ተግባር መልካም መሆኑን ገልጸው በተለይም ወጣቶች የሚያገኙትን እውቀት ወደ ገቢ ምንጭ በመቀየር የተሻለ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። መረጃው የድሬዳዋ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው፡፡

Read More Âť
News

ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት (FTVTI) ከሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ ባህልና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር ይፋዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
ስምምነቱ በመደበኛና አጫጭር ስልጠናዎችን ለሶማሊያውያን ወጣቶች ደረጃውን የጠበቀና ጊዜውን የዋጀ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገብረእግዚአብሔር እና የሶማሊያ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ሀሰን ናቸው።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ደረጃ ለማሻሻል ለሰልጣኞችና ለአሰልጣኞች ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ እንደ ትልቅ ምዕራፍ በሚቆጠረው በዚህ ስምምነት መሰረት፤ ኢንስቲትዩቱ ለ25 ሶማሊያውያን ተማሪዎች የቅድመ-ምረቃ (Bachelor’s degree) የነፃ ትምህርት ዕድል ሰጥቷል።
ይህም ኢንስቲትዩቱ ለጎረቤት ሀገራት የላቀ የስልጠና እድሎችን ተደራሽ ለማድረግ የያዘው ተልዕኮ አካል መሆኑ ተገልጿል።
ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም አክለውም፤ ይህ ስምምነት የኢንስቲትዩቱ የቀጣናዊ ትስስር ስትራቴጂ ዋና አካል መሆኑንና የአቅም ግንባታ መርሃ ግብሩም ወደፊት በስፋት እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

Read More Âť
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ሪፎርም ትግበራ ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆኑ ተገለጸ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ሪፎርም ትግበራ ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆኑ ተገለጸ
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በመገኘት፣ ተቋሙ የጀመረውን የተቀናጀ የሪፎርም እሳቤ እና ወደ ተግባር ምዕራፍ የተሸጋገሩ ሥራዎችን የመስክ ምልከታና የድጋፍ ሥራ አከናውኗል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባደረገው ቆይታ፣ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥና የአስተዳደር ማሻሻያ ተግባራትን ወደ ወሳኙ “የተግባር ምዕራፍ” ማሸጋገሩን አረጋግጧል።
ይህም ሚኒስቴሩ እንደ ሀገር የተቀመጠውን የሪፎርም ግብ ለማሳካት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና ለሌሎች የመንግስት ተቋማትም አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።
ዲጂታላይዜሽን እና የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO) በምልከታው ወቅት ሚኒስቴሩ ውጤታማ በሆነ መንገድ እየተገበራቸው የሚገኙ ቁልፍ ሥራዎች በበጎ ተነስተዋል፡፡
ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ዜጎች ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና እንግልት የሌለበት አገልግሎት የሚያገኙባቸው አሰራሮች መዘርጋቱም ተገልጿል፡፡
የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም ተቋማዊ ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ የማድረግ ሂደት ትልቅ እመርታ አሳይቷል።
ሚኒስቴሩ የሪፎርም እሳቤዎችን እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በዋናው መስሪያ ቤት ብቻ ሳይወሰን፣ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በማውረድ ክልሎችን ለማብቃት እያደረገ ያለው ድጋፍ የሪፎርሙን ውጤታማነት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተጠቁሟል። በክልሎች ደረጃ የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎች መጀመራቸውም እንደ አንድ ትልቅ ጥንካሬ ተነስቷል።
በትግበራ ምዕራፍ የታቀዱ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ወደ ቀጣዩ “የማፅናት ምዕራፍ” ለመሸጋገር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚገባ በኮሚሽኑ ድጋፍና ክትትል ቡድን ተጠቁሟል፡፡

Read More Âť
News

ሪፎርሙን በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ ለማስገባት…

ሪፎርሙን በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ ለማስገባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
በሥራና ክህሎት ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ የምክክር እና የአቅም ግንባታ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የክልል ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ጨምሮ የሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እና የሚኒስቴሩ የሪፎርም ትግበራ አስተባባሪ አቶ ጌታቸው ነጋሽ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በበጀት ዓመቱ ሪፎርሙን ሙሉ ለሙሉ ወደ ትግበራ ለማስገባት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በመጀመሪያ ዙር በሙከራ ትግበራ ደረጃ ከተመረጡ ስምንት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች መካከል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በዝግጅት ምዕራፍ የተሰጡትን ተግባራት በከፍተኛ ውጤታማነት ማከናወኑ ተጠቁሟል።
ሚኒስቴሩ በሪፎርም ትግበራው ውጤታማ እንዲሆን በዘርፉ ተግባራዊ ማድረግ የጀመራቸው ኣዳዲስ እሳቤዎችን ጉልህ ፋይዳ እንደነበራቸው አስታውሰዋል፡፡
የሪፎርሙ መነሻ የሲቪል ሰርቪሱ ዘርፉ ያለበት ነባራዊ ሁኔታ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሩ ይህ ሪፎርም በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ወሳኝ ነው ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል፡፡
የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የበቃ የሰውኃይል ፣ ብቁና አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለዜጎች የሞላባት ሀገር ለመፍጠር ሚኒስቴር መ/ቤቱ የያዘውን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ለትግበራው በቂ ዝግጅት ማደረግ ወሳኝ መሆኑ በአፅንኦት ተነስቷል፡፡

Read More Âť
News

አዲሱ የዘርፉ እሳቤ የታደገው ተቋም

አዲሱ የዘርፉ እሳቤ የታደገው ተቋም
ከዓመታት በፊት ባሳየው ዝቅተኛ አፈፃፀም ለመዘጋት ከጫፍ ደርሶ ነበር፡፡ የሚጠበቅበትን ብቃት ማረጋገጥ ባለመቻሉም አሰልጣኞችም ሆነ ሰልጣኞች በእጅጉ ተስፋ የቆረጡበትን ጊዜም አሳልፏል፤ የአሶሳ ፖሊቴክኒክ ኮለጅ!
በተቋሙ አስተዳደር ላይ በተደረጉ ለውጦችና በተሠሩ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች ከነበረበት ችግር እንዲያገግም ማድረጉን የኮሌጁ ዲን አቶ ተመስገን ሀይሉ ይናገራሉ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተቀርፆ ወደ ሥራ የገባው የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አዲስ አሳቤ ደግሞ ኮሌጁን ለዓመታት የተጫነውን ችግር ፈንቅሎ ለመውጣት ያስቻለው ብርቱ አቅም ሆኖታል፡፡
ዕቅዱን እንደ አዲስ መከለስ ኮሌጁ እሳቤውን ለመተግበር የወሰደው ቀዳሚ እርምጃ ነበር፡፡ ኮሌጁን ለአሰልጣኝ መምህራንና ለሰልጣኞች ምቹ የማድረግ ብሎም ወርክሾፖቹን የማጠናከር ሥራ ጎን ለጎን ተከናወኗል፡፡
አዳዲስ ሃሳብ ያላቸው ሰልጣኞች ሃሳቦቻቸውን የሚያሳድጉበት፣ የሚያጎለብቱበትና ወደ ተግባር የሚቀይሩበት የኢንኩቤሽን ማዕከልም በኮሌጁ ተቋቁሟል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን የኩባንያዎች መፈልፈያ ማድረግ የአዲሱ የዘርፉ እሳቤ አንዱ ዘረመል መሆኑን መነሻ በማድረግ ኮሌጁ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ወደ ምርት ገብቷል፡፡ በዚሁ መሰረት ለአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት የሚሆን ቴራዞ እያመረተ በማቅረብ 17 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ችሏል፡፡ የገጠር ሞዴል መንደሮች ግንባታ የሚውሉ 2መቶ ሺ ጡቦችን እንዲያመርት በክልሉ መንግስት በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ የኮሌጁ ዲን አቶ ተመስገን ሀይሉ ይገልፃሉ፡፡
በምርት ሂደቱ ላይ መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች እንዲሳተፉ መደረጉም የተሟላ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ አስችሏቸዋል፡፡
የቴራዞና የጡብ ምርት ቅንብር(ratio ) የሚሰሩት አሰልጣኝ መምህራን መሆናቸውና የምርት የጥራት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ከአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ማግኘታቸው የምርታቸው ጥራት በገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዳደረጋቸው የኮሌጁ ዲን ይናገራሉ፡፡
736 ነባር ሰልጣኝ ያለው የአሶሳ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በያዝነው የትምህርት ዘመን የቅበላ አቅሙን በማሳደግ 736 አዳዲስ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ ስልጠናው ፍላጎት መር እንዲሆን ለማስቻል አዳዲስ ሰልጣኞች የባዮሜትሪክስ ምዘና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡
የኮሌጁን አሠራር ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ መሠረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ‹‹የሥልጠና ጥራት የተረጋገጠበት፣ አካባቢውን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎች በስፋት የሚፈልቁበትና ሥራ ላይ የሚውሉበት ተወዳዳሪና ምርታማ ተቋም የመሆን›› ግባቸውን ለማሳካት መላ የኮሌጁ ማህበረሰብ ቀን ከሌት በትጋት እየሰሩ እንደሚገኙም የኮሌጁ ዲን አቶ ተመስገን ኃይሉ ይናገራሉ፡፡

Read More Âť
News

የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና የዲጂታል ክህሎት እንድናጎለብት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል

የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና የዲጂታል ክህሎት እንድናጎለብት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል
የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና ከዘመኑ ጋር አብረን መራመድ የሚያስችለንን የዲጂታል ክህሎት እንድናጎለብት ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ሲሉ በመዲናዋ የኮደርስ ሰልጣኞች ገለጹ።
ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውንና እውቀታቸውን እንዲያዳብሩ መንግስት የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር ዘርግቶ ብዙዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡
ኢዜአ ስልጠናውን በመውሰድ ተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶችንና የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበርን አነጋግሯል።
ማህበሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር ወጣቶች የዲጂታል እውቀታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያስችል ስልጠና እንዲወስዱ እያገዘ እንደሚገኝም አስታውቋል።
ወጣት ደረጄ ማሞ ማህበሩ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የምንወስድበትን ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ብሏል፡፡
በማህበሩ እገዛ የዲጂታል ክህሎቱን ለማሳደግ የሚያግዘውን የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ ራሱን ለማሻሻል መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
በዚህም ከኮደርስ መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነውን ዌብ ፕሮግራሚንግ በመምረጥ ስልጠና እየወሰደ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ ዘገባው የኤዜአ ነው።

Read More Âť
News

በክልሉ የ100 ቀን ዕቅድ ውስጥ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ በንቅናቄ …

በክልሉ የ100 ቀን ዕቅድ ውስጥ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ በንቅናቄ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው – ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ
የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ከኢፌደሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ቡድኑ በክልሉ ያደረገውን የድጋፍና ክትትል ሥራን አጠናቆ ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በተገኙበት ግብረ-መልስ ሰጥቷል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፤ በአፈጻጸም የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል እና በእትረት የተለዩ ጉዳችን ለማሻሻል በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ከክህሎት ልማት፣ ከሥራ እድል ፈጠራ፣ ከአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት እንዲሁም ከተቋም ግንባታ አንፃር የቀረቡ ጉዳዮች አፈጻጸም በጥንካሬና እንዴ ተሞክሮ መቅረቡን ጠቁመው በቀጣይም የሚደረግ አሰፈላጊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።
ክልሉ የዜጎችን ኑሮን ለማሻሻል የ100 ቀን እቅድ አቅዶ በትኩረትና በንቅናቄ የሚመሩትን ተግባራት በመለየት ወደ ሰራ መግባቱን ጠቅሰው በትኩረትና በንቅናቄ እንዲመራ አቅጣጫ ከተቀመጠባቸው ተግባራት መካከል የሥራና ክህሎት ቢሮ ተግባራት ውስጥ የክህሎት ልማትና የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች መሆናቸውን ገልጸዋል ።
በሱፐርቪዥን ቡድኑ የቀረበውን ግብአት መነሻ በማድረግ ልዩ እቅድ በማዘጋጀት መስራት ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በበኩላቸው፤ በክልሉ በነበራቸው የአጭር ጊዜ ቆይታ በክልሉ በሁሉም ዘርፍ ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንና እንደተሞክሮ መቀመር ያለባቸው አፈጻጸሞች ተለይተው መያዛቸውን ተጠቁመዋል። መረጃው የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው

Read More Âť
News

🔊🚨አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት‼️

🔊🚨አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት‼️
ይህ ከስር የምትመለከቱት ቻናል የሥራና ክህሎት ቴሌግራም ቻናል አይደለም! 👇
🚨 https://t.me/fdre_mols የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አይደለም! 🚨
አሁኑኑ unfollow በማድረግ ራስዎን፣ ቤተሰብዎንና ዜጎችን ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ!
ትክክለኛው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡-
✅ https://t.me/FDRE_MoLSofficial
⚠️ ጥንቃቄ
በአሁኑ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ስምና አርማ (Logo) በመጠቀም፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያወጣቸውን መረጃዎች በማባዛትና በማስመሰል የሚንቀሳቀሱ በርካታ ሀሰተኛ የቴሌግራም ገጾች እንዳሉ ደርሰንበታል።
እነዚህ አጭበርባሪ አካላት ተገልጋዮችን የሚያታልሉባቸው መንገዶች፦
👉የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ሽፋን በማድረግ በውስጥ መስመር (Inbox) ያነጋግሩዎታል፣
👉ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደተደወለ በማስመሰል ያልተገባ የገንዘብ ክፍያ ይጠይቃሉ፣
👉የተለያዩ የሐሰት ተስፋዎችን በመስጠት ንፁሃን ዜጎችን ለከፍተኛ ምዝበራ እየዳረጉ ይገኛሉ፣
ትክክለኛውን ገጽ እንዴት መለየት ይቻላል?
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይፋዊ ገጽ የሚከተሉት መለያዎች አሉት፦
✅ሰማያዊ የማረጋገጫ ምልክት (Verified Badge) ያለው ነው፣
✅ከ 47 ሺህ በላይ ተከታዮች አሉት፣
✅ማንኛውም ይፋዊ መረጃ በድረ-ገጻችንና በሌሎች የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ላይ ከሰፈሩት አድራሻዎች ጋር የተናበበ ነው፣
🛡 ሌሎችንም ይታደጉ
👉መረጃ ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ፣
👉በስህተት ሀሰተኛ ገጾችን እየተከታተላችሁ ያላችሁ ተገልጋዮች፣ በአስቸኳይ ከገጾቹ በመውጣት (Unfollow በማድረግ) ራሳችሁንና ወገኖቻችሁን ከማጭበርበር ይታደጉ፣
👉መሰል አጭበርባሪ ቻናሎች ካጋጠምዎ መረጃውን ያድርሱን!
✅ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ሁልጊዜ ይፋዊ ገጾቻችንን ብቻ ይከታተሉ!
ጥር 12/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
🔗 ለወቅታዊ ትኩስ መረጃ
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE

Read More Âť
News

ማብቃት ላይ ያተኮረ ድጋፍና ክትትል…

ማብቃት ላይ ያተኮረ ድጋፍና ክትትል
የሥራና ክህሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚያካሄደውን ድጋፍና ክትትል እና የመስክ ምልከታ አስመልክቶ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ በሥራው ለሚሳተፉ አካላት ኦረንቴሽን ሰጥተዋል፡፡
የመስክ ምልከታው ሚኒስቴሩ በዘርፉ የቀረጻቸው እሳቤዎች አተገባበር፣ ከአፈጻጸም አኳያ ወደኋላ የቀሩትን መደገፍ፣ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ሪፎርም ላይ ግንዛቤ ማስጨበጥ እንዲሁም በክህሎት ልማት፣ በሥራ ሥምሪት፣ በአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍና በተቋም ግንባታ ዘርፎች የተገኙ ልምዶች እና ተሞክሮዎች ቀምሮ ለማስፋት ያስችላል ተብሏል፡፡
በተጨማሪም በበጀት አመቱ የተያዙ ትላልቅ ግቦችን ለማሳካት የተደረገው ዝግጅትና በግማሽ አመቱ የተከናወኑ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች የምልከታው አካል እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡
ድጋፍና ክትትሉ ከጥር 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን በሂደቱ የሚገኙ ምርጥ ተሞክሮዎች የመቀመርና የማስፋት ስራም እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡

Read More Âť
News

ድህነትን የምናሸንፈው በእውቀት፣ በክህሎት እና በጠንካራ ሥራ ነው! — ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ

ድህነትን የምናሸንፈው በእውቀት፣ በክህሎት እና በጠንካራ ሥራ ነው! — ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
ድህነትን በዘላቂነት ማሸነፍ የሚቻለው በእውቀት፣ በክህሎት እና በጠንካራ የሥራ ባህል መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለጹት፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በዘርፉ አዳዲስ እሳቤዎችና መመሪያዎች ዙሪያ በአማራ ክልል በጎንደር እና በደብረብርሃን ክላስተር ለሚገኙ የዘርፉ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫና የሥልጠና መድረክ ላይ ነው።
በመድረኩ በሥራ ዕድል ፈጠራ መስክ የተቀረጹ አዳዲስ እሳቤዎች፣ የአሠራር ሥርዓቶችና መመሪያዎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የሥራ አጥነት ችግር ዋነኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ፈተና መሆኑን በማንሳት፣ መንግሥት የሥራ አጥነት ምጣኔውን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ በልዩ ትኩረት እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያውያን ፖለቲካዊ ነፃነታችንን በማስከበር ረገድ ደማቅ ታሪክ ያለን ሕዝቦች ነን ያሉት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነታችንን ሙሉ በሙሉ ባለመጎናጸፋችን፣ ድህነት በዓለም አደባባይ አንገታችንን ቀና እንዳናደርግ አድርጎን ቆይቷል ብለዋል።
ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ መንግሥት ትልቅ ርዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የቀረጻቸው አዳዲስ እሳቤዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት መስኩ ተስፋ ሰጪና ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አመላክተዋል።
በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ የታቀዱ የሪፎርም አጀንዳዎችን ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ባለሙያ የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
የአማራ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶ/ር ስቡህ ገበያው በበኩላቸው፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ በዘርፉ አዳዲስ እሳቤዎች ላይ ለአመራሩና ለባለሙያዎች ተቀራራቢ ግንዛቤ ለመፍጠር መድረኩን በባዘጋጀቱ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top