Mols.gov.et

mols mols

News

አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት!

አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት!
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል (Future Fit International) እና ከካናዳ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ካናዳ ለመላክ የሚያስችል ስምምነት ሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም መፈራረሙ ይታወሳል።
👉 ሆኖም ይህንን ተከትሎ፣ አንዳንድ ሕገ-ወጥ አካላት የሚከተሉትን የፈጠራ ወሬዎች በማህበራዊ ሚዲያ እያሰራጩ ይገኛሉ፦
• ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI/Deepfake) በመጠቀም የተፈበረኩና አሳሳች ምስሎችንና በቨዲዮዎችን ማሰራጨት 📽️
• “ምዝገባ ተጀምሯል” የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመልቀቅ ማህበረሰቡን ማደናገር፣
• በግል ስልክ ቁጥሮች ደውሉ በማለት ዜጎችን ለኢኮኖሚያዊ ብዝበዛ መጋበዝ 📞
እነዚህ ማስታወቂያዎች ሙሉ በሙሉ የማጭበርበር ተግባራት መሆናቸውን እናሳውቃለን። 🚫
❗ ትኩረት የሚሹ ነጥቦች፦
• በአሁኑ ወቅት ለካናዳ የሥራ ስምሪት ምንም አይነት ይፋዊ ምዝገባ አልተጀመረም፣
• በግል ስልክ ቁጥሮች የሚደረጉ ጥሪዎችም ሆኑ የሚላኩ አጫጭር መልዕክቶች (SMS) ሚኒስቴሩን አይወክሉም!
✅ የምዝገባ ጥሪ የሚደረገው
👉በብሔራዊ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያዎች፤
👉የሚኒስቴሩን ይፋዊ የማረጋገጫ ምልክት (Blue Badge) ባላቸው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ብቻ
🚫 ሊወሰዱ የሚገቡ ጥንቃቄዎች
• ለማያውቁት ወይም በግል ስልክ ቁጥር ለሚደረግ ጥሪ ምላሽ አይስጡ፤
• በማንኛውም ሁኔታ የገንዘብ ክፍያ አለመፈጽም፤
• ምንጫቸው ያልተረጋገጡ መረጃዎችን በማሰራጨት የጥፋቱ ተባባሪ አይሁኑ
✅ ምን ማድረግ ይገባዎታል?
✔️ መረጃዎችን ከሚኒስቴሩ ይፋዊ የመገናኛ ዘዴዎች ብቻ ያረጋግጡ፤
✔️ አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ( 9138 በነፃ የስልክ መስመር ወይም info@mols.gov.et ) እና በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የህግ አስከባሪ አካላት ይጠቁሙ።
📢 አስቸኳይ
📍 ዜጎች ከዲጂታል ማጭበርበርና ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን!

Read More Âť
News

የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን ከዕቅድ በላይ ማሳካቱን ቢሮው አስታወቀ

የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን ከዕቅድ በላይ ማሳካቱን ቢሮው አስታወቀ
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ10 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ጋር ገምግሟል።
በዚህም ለ320,000 በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስታውቋል። ይህም ከዕቅዱ አኳያ 111 በመቶ እንደሆነ ነው የተገለፀው።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ትልቁ ሪፎርም መዋቅር መቀየር ሳይሆን በአመራሩና በአስተግባሪው ዘንድ የሚፈጠር የአስተሳሰብ ለውጥ ነው ብለዋል።
በሥራ ዕድል ፈጠራ ወቅት የሥራ ማማረጥ ችግር እንደ ዋነኛ ተግዳሮት የታየ መሆኑን አመላክተው ቢሮው ለወላጆችና ለሥራ ፈላጊዎች የአመለካከት ቀረጻ ንቅናቄ መደረጉ ትርግም ያለው ውጤት ማምጣቱን አመላክተዋል።
ባለፉት 10 ወራት በቢሮው ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው የ2.2 ቢሊዮን ብር የብድር አቅርቦትና የሥራ ቦታዎች ማመቻቸት መቻሉን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Read More Âť
News

የሥራ ቦታዎች ምቹ መሆን ለምርታማነትና ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የሥራ ቦታዎች ምቹ መሆን ለምርታማነትና ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
‎
‎በኢትዮጵያ የቡና እና የሆርቲካልቸር የዕሴት ሰንሰለቶች ውስጥ ምቹ የሥራ ሁኔታን (Decent Work) ለማረጋገጥና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የተዘጋጀው ሀገራዊ የፕሮጀክት ዓብይ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል።
‎የሥራ ቦታዎች ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ ምርትና ምርታማነትን ከማረጋገጥ ባለፈ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትንና ተገቢውን የገበያ ድርሻ ለማግኘት ያስችላል ሲሉ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ገልፀዋል።
‎በኢትዮጵያ ቡና እና ሆርቲካልቸር የዕሴት ሰንሰለቶች ምቹ የሥራ ሁኔታን ማሻሻል ፕሮጀክት በአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና በዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት (ILO) አማካኝነት በኦሮሚያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያና ከሲዳማ ክልሎች ይተገበራል፡፡
‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ምቹ የሥራ ሁኔታን (Decent Work) በሀገሪቱ ለማረጋገጥ የአምስት ዓመት ስትራቴጂ ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል።
ይህም በአዲሱ የሪፎርም አስተሳሰብ የሥራ ቦታዎች ሰላምን በማረጋገጥ፣ የሠራተኞችን ደህንነትና ጤንነት በመጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ የሚያጠናክር ነው።
‎
‎በመድረኩ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ የሚመለከታቸው ሚኒስቴር መ/ቤቶችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
‎
በፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣ በአሰሪዎች፣ በሠራተኞች እና በአጋር ድርጅቶች መካከል የሚፈጠረው ቅንጅት ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን፣ የሥራ ሁኔታ ምቹነት እንዲረጋገጥ፣ በሥርዓተ-ጾታ እኩልነት እና በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ዙሪያ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት እንዲፈቱ እንደሚያግዝ ተገልጿል።
‎
‎በመንግሥትና በማህበራዊ አጋሮች መካከል የሚፈጠር ጠንካራ ቅንጅት የግብርና ምርት ምሰሶ የሆነውን የቡና እና የአትክልት ምርቶቻችን ያለችግር ኤክስፖርት ለማድረግ የሚያስችል የ(Labor Compliance) ተፈፃሚነት በማሳደግ፣ የተሻለ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ዘላቂ የሆነ አገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ቁልፍ መሣሪያ መሆኑ ተመላክቷል።

Read More Âť
News

በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት…

በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ያሳደጉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ከንቲባ ከድር ጁሃር
በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
የሀገር ውስጥና የውጭ አገራት የስራ ስምሪትን ለማመቻቸት ያለመ የአሰሪና ሰራተኞች አገናኝ ዐውደ ርዕይ ዛሬ በድሬደዋ ተካሂዷል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንዳሉት በድሬደዋ የወጣቶችን የስራ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በሌሎችም ዘርፎች አማራጮችን በማስፋት ላይ ይገኛል።
ተግባሩን ለማስቀጠልም ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት በተለያዩ የሙያ መስኮች የሰለጠኑ 350 ወጣቶች በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የስራ እድል እንዲያገኙ መደረጋቸውን ገልጸው፤ ለዚህም የዛሬው መርሃ ግብር መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ የስራ ስምሪት ለሚሳተፉ ወጣቶችም በአሰሪና ሰራተኞች አገናኝ ድርጅቶች አማካኝነት 380 ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ወጣቶች በዕውቀትና በክህሎት ተወዳዳሪ በመሆን የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም ሴክተር መስሪያቤቶች እና ባለሃብቱ በቅንጅት እንዲሰሩ የተለያዩ መድረኮች መካሄዳቸውን ጠቁመው የአሁኑ ዐውደ ርዕይም የቅንጅታዊ ስራው ማሳያ ነው ብለዋል።
ከሀገር ውስጥ የስራ ስምሪት ባለፈ ወደ ውጭ ሀገራት ለሚጓዙት ወጣቶች የቋንቋ፣ የአካባቢዎቹ መረጃዎችና ሙያዊ ስነምግባር ላይ ተገቢውን ስልጠና በመውሰድ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ መሰራቱን አንስተዋል። ዘገባው ኢዜአ ነው።

Read More Âť
News

በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ

በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ ለ90 ወጣቶች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የመሸጫና የመሥሪያ ቦታ ሼድ አስረክቧል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላ ይህ ተራ ላሜራ ወይም የመሸጫና የመሥሪያ ቦታ ሳይሆን ትልቁ የቢዝነስ ማዕከል ይሆናል ብለዋል።
የብልፅግና ፓርቲ ትልቁ ዕሳቤ የሰውን ህይወት መቀየርና ዜጋን ውጤታማ እንዲሆን ማድረግ ነው ብለዋል።
ሰው ምርታማነትና ፍሬያም እንዲሆን ማድረግ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ፋይዳ አለው ያሉት ኃላፊው፥ ስራን መፍጠር ምርታማነት ማሳደግ እንደሆነም ገልፀዋል።
የስራ ትንሽ የለውም ያሉት ኃላፊው፥ ወጣቶች ስራን ሳይንቁ መሰራትና መትጋት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
ለወጣቱ ስራ ዕድልን ለመፍጠር የግሉ ሴክተርን ማጠናከር ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው፥ ስራ አጥነትን ለመቅረፍ እያንዱንዱ ሰው ምሳሌ የሚሆን ስራ በመሰራት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበትም አሳስበዋል።
ሥራ አጥነት ችግር ለመንግስት ብቻ ሸክም ሳይሆን ለሁሉም ነው ያሉት ኃላፊው፥ ወጣቶች ስራን እንዲፈጥሩ ማበረታታት ያስፈልጋል ብለዋል።
ወጣቶቹ በማደራጀት፣ በማሰልጠን እንዲሁም አስፈላጊውን ቁሳቁስ በማሟላት በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ርብርብ ያደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችና እምቅ አቅሞቻችን በመጠቀም ለወጣቱ የተለያዩ ስራ አማራጮችን ለመፍጠር ልዩ ትኩረት መስጠት እንዳለበትም አሳስበዋል።
የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘካሪያስ ጃታ የከተማው አስተዳደር ለወጣቱ ስራ ዕድል ለመፍጠር የ90 ቀናት ዕቅድ በማቀድ ስሰራ እንደቆየ አስታውሰዋል።
ወጣቶች በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍና የክህሎት ስራ ዕድል መፍጠሩን የገለጹት ከንቲባው፥ ይህ ለወጣቱ ተስፋ የሚጭር ነው ብለዋል።
በከተማው የሚገኙ ሌሎች ወጣቶች ተደራጅተው መንግስት ያመቻቸው የስራ ዕድል ተጠቅመው ለመሰራት ፍቃደኛ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
በዘርፉ የተሰማሩ ወጣቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ይህ መነሻ ይሆናል ያሉት ከንቲባው፥ ሌሎች ትምህርት የሚሆን ስራዎች መሰራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
ዘገባው የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው።

Read More Âť
News

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን የማዘመን ጉዞ

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን የማዘመን ጉዞ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እንደ አዲስ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ እየተገበራቸው በሚገኙ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች በርካታ ዜጎች ክብርና ደህንነታቸው ተጠብቆ በውጭ ሀገራት ከሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ።
ሥርዓቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረግ፣ የውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት አዋጁን ማሻሻል ፣ አዋጁን ለመተግበር የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀት ፣ የአስፈፃሚና ባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ ማሳደግ የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት ከተከናወኑ ተግባራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
በተሻሻለው አዋጅ መሰረት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎችን እንደ አዲስ የመመዝገብና አሰራራቸውን እንዲያዘምኑ የማገዝ ሥራ እየተሰራም ይገኛል ።
በዚሁ መሰረት በደረጃ አንድ የተመዘገቡ ኤጀንሲዎች የቢሮ አደረጃጀታቸውን እና የአገልግሎት አሠጣጣቸውን በሚጠበቀው ደረጃ እያዘመኑ እንደሚገኙ በሚኒስቴር መ/ቤቱ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ይገኛል ።

Read More Âť
News

16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር ተጠናቀቀ

16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር ተጠናቀቀ
ላለፉት ቀናት በአራዳ ፓርክ “የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና” በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የቆየው 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አውደ-ርዕይና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር በደማቅ ሥነ-ስርዓት ተጠናቋል።
በማጠቃለያ መርሐ ግብሩ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ፤ የቴክኖሎጂ ታሪክ የኢኮኖሚ ልማት ታሪክ መሆኑን በጥልቀት በመተንተን፣ ባለፉት ቀናት የቀረቡት የፈጠራ ሥራዎች የሀገሪቱን የልማት ተስፋና ተጨባጭ እንቅስቃሴ የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል።
መንግስት የክህሎት መር የሥራ ስምሪትን እንደ ዋነኛ ፖሊሲ በመከተሉ፣ ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም በተግባር እንዲያሳዩና በ21ኛው ክፍለ ዘመን ራሳቸውን በእውቀት፣ በክህሎትና በሥነ-ምግባር በማነጽ ለሀገራቸው ብልጽግና እንዲተጉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል።
አክለውም፣ ወጣቶች የሥራን ክብር በመረዳትና ዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ የሀገር ግንባታ አካል እንዲሆኑና የጀመሩትን የፈጠራ ሥራ ወደ ቢዝነስ በመቀየር ራሳቸውን እንዲያዘጋጁም አደራ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው አውደ-ርዕይ ቴክኖሎጂዎችን ለዕይታ ብቻ ከማቅረብ ባለፈ፣ በቀጥታ ወደ ፋብሪኬሽን ኢንጂነሪንግ በማሸጋገር ለተጠቃሚው ተደራሽ እንዲሆኑ የሚያስችል አዲስ ስትራቴጂ የተተገበረበት መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የውጭ ምንዛሬን የሚያድኑ ተኪ ምርቶችን ማምረት እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዕለቱ በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በዲጂታል አይሲቲ ቴክኖሎጂዎች ፈጠራ፣ በፋሽን ዲዛይን፣ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ከፍተኛ ውጤት እንዲሁም በስፖርት ውድድር አሸናፊ በመሆን በደረጃ ለወጡ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።
በመድረኩ የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርት መተካት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መገለጹን የቢሮው መረጃ ያመለክታል። ዘገባው የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ነው።

Read More Âť
News

ፈጠራና ፍጥነትን ማዕከል አድርጎ ተኪ ምርት ማምረት…

ፈጠራና ፍጥነትን ማዕከል አድርጎ ተኪ ምርት ማምረት ለኢኮኖሚ ሽግግሩ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የሀገር ውስጥ ምርታማነትን በፈጠራና በፍጥነት በማሳደግ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ በመተካት የኢኮኖሚ እድገቱን ማፋጠን እንደሚገባ የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለጹ።
አፈ-ጉባኤዋ ይህንን የገለፁት በሸገር ከተማ ገላን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተጀመረውን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራና የክህሎት ውድድርን ባስጀመሩበት ወቅት ነው።
የተከበሩ ወ/ሮ ሰዓዳ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ መንግስት በትምህርት፣ በሙያ ስልጠና እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመራቸው የሪፎርም ስራዎች ውጤት እያሳዩ ይገኛሉ።
በተለይም በየዓመቱ የሚፈጠሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሥራ ባህልን በመቀየር ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ እነዚህ ፈጠራዎች የሥራ ዕድልና የኢኮኖሚ ምንጭ እንዲሆኑ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የስልጠና ተቋማትም የገበያ ፍላጎትን መሠረት ያደረገ ጥናት በማድረግና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ያላቸውን ትብብር በማጠናከር፤ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል ማፍራት እንዳለባቸው ተገልጿል።
ይህም የኢኮኖሚ ሽግግሩን ከማሳለጡ ባለፈ ሀገር በቀል ዕውቀትን ወደ ምርት በመለወጥ ረገድ የጎላ ድርሻ ይኖረዋል።
የኦሮሚያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ጎልጋ በበኩላቸው፤ ቢሮው ሰፊ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማጠናከር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንንም ግብ ለማሳካት ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የክህሎት ማዳበሪያና ዘላቂነት ያላቸው ስልጠናዎች በስፋት እየተሰጡ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በ22 ክላስተሮች እና በ215 የስልጠና ተቋማት መካከል የሚካሄደው ይህ ውድድር፤ የሸገር ከተማን የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ ለተያዘው እቅድ ስኬት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በመድረኩ መገለፁን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Read More Âť
News

5ኛው ዙር ክልላዊ የቴክኖሎጂና ተግባራዊ ምርምር ውድድር ተጠናቀቀ

5ኛው ዙር ክልላዊ የቴክኖሎጂና ተግባራዊ ምርምር ውድድር ተጠናቀቀ
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ከአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሲያካሂድ የነበረው የ2018 በጀት ዓመት የ5ኛው ዙር ክልላዊ የቴክኖሎጂና ተግባራዊ የጥናትና ምርምር ውድድር ተጠናቋል፡፡
ውድድሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኢንዱስትሪና ከክልል መንግሥታት ጋር ያላቸውን ትስስር ለማጠናከርና የምርምር ውጤቶች በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ የሚወርዱበትን ዕድል ለመፍጠር ያስቀመጠውን አቅጣጫ መሠረት አድርጎ የተካሄደ ነው፡፡
በዳኞች ግምገማና በድምር ውጤት መሠረት፣ የአሶሳ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እና የቡለን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአንደኝነት በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ደግሞ የሦስተኛ ደረጃን በመያዝ የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ መሆን ችሏል፡፡
ቢሮው ለአሸናፊዎቹ እንደየደረጃቸው ከ15ሺህ እስከ 25ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ማበረታቻና የዕውቅና ምስክር ወረቀት በማበርከት ኮሌጆቹ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲያሳድጉ አበረታቷል፡፡
የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም ሸንገል በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፣ ቴክኖሎጂ ለሀገርና ለክልል ልማት የማይተካ ሚና አለው፡፡ እንዲህ ያሉ ውድድሮች በወጣቶችና በተመራማሪዎች ዘንድ የፈጠራ ባህልን ለማዳበር እና ተግባራዊ ምርምሮችን ወደ ምርታማነት ለመቀየር ወሳኝ መድረኮች መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡
የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያለውን ይህን ውጤታማ ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው አረጋግጠዋል።
በተለይም አሶሳ ግብርና ኮሌጅ በአንደኝነት እንዲያሸንፍ ያስቻለው “Improving organic farming practice by using vertical farming” በሚል ርዕስ ያቀረበውና በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመፍታት ያለመው የምርምር ሼል በዳኞች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆት ተችሮታል፡፡
ተመራማሪዎቹና የኮሌጁ አመራሮች በበኩላቸው የተገኙ ውጤቶችን ወደ ማህበረሰቡ የማሸጋገርና በሀገር አቀፍ ደረጃም የተሻለ ውጤት የማስመዝገብ ሥራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ዘገባው የቤኒሽንጉል ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው

Read More Âť
News

ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ. . .

ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ ያገኘውን ክህሎት ለእድገት በተግባር መተርጎም ይጠበቅበታል
ትውልዱ በቴክኒክና ሙያ መስክ የሚያገኛቸውን ክህሎቶች በተግባር በመተርጎም ለእድገት የበኩሉን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ100ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዩቤልዩ በዓል የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት “ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ ለቀጣዩ ትውልድ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች አከብሯል።
በሥነ-ሥርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጁ መምህራንና ተማሪዎች፣ የቀድሞ ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኮሌጁ የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አውደ-ርዕይ፣ የኪነ-ጥበብ ስራዎችና የባህል አልባሳት ትዕይንት ቀርበዋል።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሚደቅሳ ከበደ በዚሁ ወቅት፤ የከተማ አስተዳደሩ የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ብቁ ሙያተኛ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ሰልጣኞች በቂ ክህሎት እንዲጨብጡ ከኢንዱስትሪዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ከቴክኖሎጂ ዕውቀት ውጪ ልማትና ዕድገት ማረጋገጥ እንደማይታሰብ ጠቁመው፤ በዚህ በኩል ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
በዓሉን ከማክበር ባለፈ በቴክኒክና ሙያ መስክ የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
oroORO
Scroll to Top