Mols.gov.et

News

News

ምርትና ምርታማነትን ማጎልበት

ምርትና ምርታማነትን ማጎልበት፣ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ማመንጨትና ከባቢያዊ ችግሮችን መፍታት የሚጠበቅባቸው የቴክኒክና ሙያ ተቋማት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ከሥልጠና ማዕከልነት ባለፈ የኩባንያዎች መፈልፈያ፣ የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች መፍለቂያና የሥራ ዕድል ፈጣራ ማዕከላት እንዲሆኑ የሚያስችል አዲስ እሳቤን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
የዚህ እሳቤ ዋንኛ ዓላማ የስልጠና ተቋማቱ ያላቸውን ማሽኖችና ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም ከባቢያዊ ችግርን የሚፈቱ ምርቶችን እንዲያመርቱ ፣ በሂደቱም በተግባር በተደገፈ መልኩ ሰልጣኞቻቸውን በክህሎት እንዲያበቁ ማስቻል ነው፡፡
በዚህ መሰረት በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ራሱን የቻለ ህጋዊ ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው ወደ ሥራ እየገቡ ይገኛሉ፡፡
የመሰል ኢንተርፕራይዞች መቋቋም ተቋማቱ የውስጣዊ ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ፣ ምርትና ምርታማነትን እንዲያጎለብቱና አዳዲስ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በማመንጨት የአካባቢቸውን ችግር እንዲፈቱ የሚያስችል አቅምን እንደሚያላብሳቸው ይጠበቃል፡፡

Read More Âť
News

የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ሀገር በቀል ክህሎትን

የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ሀገር በቀል ክህሎትን በማጎልበት የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው – የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የዜጎችን የዲጂታል ፈጠራና ክህሎት ለማስፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ ነው።
በተለይም በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ሳይበር ደኅንነት ያሉ አዳዲስ የሥልጠና መርሃ ግብሮች ተቀርጸው ተግባራዊ መደረጋቸውን ጠቁመዋል።
ለዚህም የክህሎት ማበልጸጊያ ቴክኖሎጂዎችን በማሟላት የግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድንና መሰል ዘርፎችን ምርታማነት የሚያሻሽል ሀገር በቀል የፈጠራ ክህሎት እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ዕድገት መሳለጥ መሰረት መጣሉንም ዋና ዳይሬክተሩ አውስተዋል።
የ2030ው ስትራቴጂ ደግሞ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ሥርዓቱን የበለጠ በማዘመን ረገድ የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት ሀገር በቀል የፈጠራ ክህሎትን በማጠናከር ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ምርምር ውጤቶችን እንዲያፈልቁ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም የሰልጣኞችን የቅበላ አቅም በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በዘርፉ የተሰማሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎችም ስትራቴጂውና የተሰጣቸው ስልጠና ለስኬታቸው መነሻ መሆኑን ገልጸዋል። ።ዘገባው የኢዜአ ነው

Read More Âť
News

በአዲስ አበባ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት

በአዲስ አበባ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ የአሰራር ምኅዳር መፈጠሩ ተገለፀ
በአዲስ አበባ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ የአሰራር ምኅዳር መፈጠሩን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ ገለጹ።
ቢሮው በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከዛሬ መጋቢት 2/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የሥራ አውደ ርዕይ ከፍቷል።
“የግል ዘርፍ ተሳትፎ፤ የብቁ ወጣቶች ማንሰራራት ለገሀር ልዕልና” በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው የሥራ አውደ ርዕይ ላይ 6ሺህ የሚሆኑ ሼል ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች ቀጥተኛ ሼል ዕድል ተጠቃሚ የሚሆኑበት ዕድል እንደሚመቻች ተገልጿል።
የሥራ አውደ ርዕዩን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መርቀው ከፍተውታል።
በዚሁ ጊዜ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ እንዳሉት፤ የአዲስ አበባ ከተማ ፈጣን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድገት ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት መሰረት እየጣለ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ሥራ ፈላጊዎችን በማደራጀት ከሥራ ቀጣሪዎች ጋር በማገናኘት የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ ዘርፍም ሥራ ፈላጊዎችና ቀጣሪዎችን የሚያገናኝ ምቹ ምህዳር መፍጠር መቻሉን አስረድተዋል።
የአዲስ አበባ የ24/7 የሥራ ባህልም የከተማዋን ልማትና ዕድገት በማስቀጠል የበርካታ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የቢሮ ምክትልና የምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ አስፋው ለገሰ በበኩላቸው፤ በሰባት ወራት ውስጥ ከ280ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሥራ አውደ ርዕዩ የሚሳተፉ ከ200 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶች የሚያስፈልጋቸውን የሰለጠነ የሰው ሃይል በመመልመል በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ዘገባው የኢዜአ ነወ።

Read More Âť
News

በኦሮሚያ ክልል የእሴት ሰንሰለትን መሰረት በማድረግ …

በኦሮሚያ ክልል የእሴት ሰንሰለትን መሰረት በማድረግ በርካታ የሥራ ዕድሎችን ለዜጎች መፍጠር እንደተቻለ ተገለፀ
የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና የክህሎት ቢሮ፣ የከተማ ሥራ ዕድል ፈጠራና ህጋዊነት ዳይሬክተር አቶ ተማም ሁሴን እንደሚገልፁት በክልሉ በዶሮ እርባታ፣ በከብት ማድለብ፣ በንብ ማነብና በመሳሰሉት ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራዞችን በእሴት ሰንሰለት የማስተሳሰርና ውጤታማነታቸውን የማረጋገጥ ሥራ እየተሠራ ይገኛል፡፡
በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች እንቁላል አስፈልፍለው የአንድ ቀን ጫጩት የሚያስረክቡ፣ የእንቁላልና ሥጋ ዶሮዎችን የሚያረቡና ለገበያ የሚያቀርቡ ኢንተርፕራይዞችን በእሴት ሰንሰለት ለማስተሳሰር በተሠሩ ሥራዎች በርካታ ቁጥር ላላቸው ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አቶ ተማም ይናገራሉ፡፡
የትስስሩን ውጤታማነት ለማረጋገጥም የብድር፣ የማምረቻና መሸጫ ቦታ አቅርቦት የማመቻቸት ሥራ በሥፋት እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን በዶሮና በከብት መኖ ምርት ላይ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንስን በመጠቀም ማሽኖች እየቀረበ እንደሚገኝም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
በተመሳሳይ የእንስሳ መኖ ዝግጅት ጀምሮ በወተት ከብት እርባታና የወተት ተዋፅኦን አቀነባብረው ለገበያ የሚያቀርቡ ኢንተርፕራይዞችን ለማስተሳሰር እንዲቻልም የከብት እርባታ የክላስተር ማዕከላትን በሁሉም የኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዞኖችና ወረዳዎች የማስፋት ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
በቀጣይም በኢንተርፕራይዝ ተደደራጅተው በወል ቦታዎች ላይ የስንዴ እያመረቱ የሚገኙ ወጣቶችን ዱቄት፣ ዳቦና ኬክ ከሚያመርቱና ለገበያ ከሚያቀርቡ ኢንተርፕራይዞች ጋር የማስተሳሠር ሥራ ለመሥራት የሚስችል ዕቅድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝም ጠቁመዋል ፡፡
ኢንተርፕራይዞችን በግብዓትና ምርት አቅርቦት በማስተሳሰር በርካታ የሰው ኃይልን ተሳታፊ የሚደርግ የሥራ ዕድል የመፍጠር ግብ ያለው ‹‹እሴት ሰንሰለትን መሰረት ያደረገ የሥራ ዕድል ፈጠራ›› በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተቀረፀው የዘርፉ አዲስ እሳቤ ውስጥ ከተካተቱ ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Read More Âť
News

“የኢንዱስትሪ ሰላም ለምርታማነት፣ ምርታማነት ለሀገራዊ ብልጽግና!”

“የኢንዱስትሪ ሰላም ለምርታማነት፣ ምርታማነት ለሀገራዊ ብልጽግና!”
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን እና ለምርታማነትና ተግዳሮት የነበሩ ትርክቶችን ለመቀየር የሚያስችል አዲስ የሪፎርም እሳቤን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢንዱስትሪ ግንኙነት ዴስክ ኃላፊ አቶ ውብሸት ዘለለው የሚኒስቴር መ/ቤቱ አዲስ የዘርፍ እሳቤ የኢንዱስትሪዎችንና የሠራተኞችን ተወዳዳሪነት የሚያልቅ ብሎም አቀፋዊ ዕድሎችንና ተግዳሮቶችን በአግባቡ የቃኘ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
በኢትዮጵያ ሾለ ምርታማነት የሚነሱ ትርክቶች ብዙ ጊዜ በሁለት ተቃራኒ ጎራዎች እንደሚፈረጁ የሚገልጹት አቶ ውብሸት፤ በአንድ በኩል አሠሪዎች “ሠራተኛው ዝቅተኛ የሥራ ዲሲፕሊንና ክህሎት፣ የሥራ ባህል የሌለው፣ መብቱን ብቻ የሚጠይቅ፣ ግዴታውን የማይወጣና ምርታማነቱ ዝቅተኛ ነው” የሚል ትርክት እንደሚያራምዱ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ሠራተኞች “ሰብአዊ ክብራችን፣ ጤንነታችንና ደህንነታችን የማይጠበቅ እንዲሁም በሕግ የተቀመጠ መብታችንን እንዳንጠቀም ክልከላ ይደረግብናል፤ ለምርትና ምርታማነት የሚያጎለብቱ ሐሳቦች ቢኖሩንም የሚሰማን ባለመኖሩ ምርታማነታችን ቀንሷል” በሚል አሠሪዎችን ሲከስሱ ይደመጣል፡፡
መሰል አመለካከቶች ሼር መስደዳቸውና “የበዝባዥና ተበዝባዥ” ትርክት መጎልበቱ በኢንዱስትሪዎች ምርታማነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲፈጥሩና በኢንዱስትሪ ሰላም ላይ ጥላ ሲጥሉ ቆይተዋል፡፡
የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያመላክቱት ምርታማነትን ከሰው ክብርና ጥቅም ነጥሎ ማየት እንደማይቻልም የሚሉት አቶ ውብሸት ሚኒስቴሩ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትን በምርትና ምርታማነት ላይ ምክክር በማድረግ የማክሮ ኢኮኖሚ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚችል እና የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያረጋግጥ አዲስ የኢንዱስትሪ ባህል ለመገንባት ላለፉት ዓመታት “የኢንዱስትሪ ማኅበረሰብ ምክክር ለምርታማነት” ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ያስረዳሉ፡፡
ይህንንም ተከትሎ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶች በማደራደርና በማስማማት ፈጣን መፍትሔ የሚያገኙበት አሠራር በመዘርጋቱ የሥራ ማቆም አድማዎችንና የሥራ መስተጓጎሎችን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ተችሏል።
በሌላ በኩል ሠራተኛው ስለ መብቱና ግዴታው በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ በተሠሩ ሥራዎች የሥራ ተነሳሽነትንና ዲሲፕሊንን በማጎልበት የኢንዱስትሪዎችን የምርት ጥራትና ብዛት ማሳደግ ተችሏል።
ኢንዱስትሪ ማኅበረሰቡ (አሠሪ፣ ሠራተኛና መንግሥት) በጋራ በሚያደርጉት ምክክር፣ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጤቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችሉ ስልታዊ አቅጣጫዎች እየተቀመጡ ይገኛሉ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር “የኢንዱስትሪ ሰላም ለምርታማነት” የሚለውን መሪ ሃሳብ ለማሳካት፣ የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ምክክር ቀጣይነት ባለው መልኩ እስከ ታችኛው የዘርፉ መዋቅር እንዲሰርጽ በትኩረት እየሠራ መሆኑ የኢንዱስትሪው ማኅበረሰቡ ለምርታማነትና ለሀገራዊ ብልጽግና በጋራ የሚቆምበትን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር አቶ ውብሸት ዘለለው ገልጸዋል።

Read More Âť
News

ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለሀገር ምርታማነት ዕድገት

ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለሀገር ምርታማነት ዕድገት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሰላማዊ የሥራ አካባቢን በመፍጠር ምርታማነትን በማሳደግ እንዲሁም በአሠሪ፣ በሠራተኛና በመንግሥት መካከል የሚደረገውን የሶስትዮሽ ግንኙነት በማጠናከር ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች እያስመዘገበ ይገኛል።
በሚኒስቴሩ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ዘርፍ የሶስትዮሽ ግንኙነት ማስተባበሪያ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳልክ ተክለኃዋርያት እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በዘርፉ ይስተዋል የነበረው አሉታዊ ግንኙነት በአዲስ መልክ እንዲቀየር ተደርጓል።
“ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለሀገር ምርታማነት ዕድገት ወሳኝ መሠረት ነው” ያሉት አቶ እንዳልክ፣ ሚኒስቴሩ ወሳኝና አማካሪ ቦርዶችን በሁሉም ክልሎችና የኢንዱስትሪ መንደሮች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ መሆኑን አስረድተዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት ሚኒስቴሩ የቦርዶችን አቅም ለመገንባትና አሠራራቸውን ለማዘመን በርካታ ተግባራትን አከናውኗል። በዚህም መሰረት ለወሳኝ ቦርዶች የቀረቡ የወል የሥራ ክርክሮች በውይይትና በስምምነት እንዲቋጩ ተደርጓል። ይህም ሠራተኞች የሥራ ዋስትናቸው ሳይቋረጥ እንዲቀጥሉ፣ ድርጅቶችም ያለምንም መስተጓጎል ወደ ምርታማነት እንዲመለሱ አስችሏል ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

በክልሉ በ8 ወራት ከ29 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ቢሮው አስታወቀ

በክልሉ በ8 ወራት ከ29 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ቢሮው አስታወቀ
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ባለፉት ስምንት ወራት ከ29 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አስታውቋል።
ይህ አፈጻጸም ክልሉ ካስቀመጠው ግብ አንጻር ከፍተኛ ውጤት የታየበት መሆኑም ነው ቢሮው ያስታወቀው።
የቢሮው የሥራ ስምሪት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አለነ እንደገለጹት፣ ይህ ስኬት የተመዘገበው ቢሮው ተግባራዊ እያደረገ ባለው “አዲሱ የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ” እሳቤ ነው።
ስራው በዘልማድ ከመመራት ወጥቶ በዕውቀትና በክህሎት ላይ እንዲመሠረት መደረጉ ለውጤቱ መገኘት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ኃላፊው አብራርተዋል።
የተፈጠሩት የሥራ ዕድሎች ሁሉንም የኢኮኖሚ ዘርፎች ያካተቱና ፍትሃዊነትን የተከተሉ መሆናቸውንና በቴክኒክ ኮሚቴው መካከል ያለው የተቀናጀ አሠራር ለሥራው መፋጠን ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱም ነው የተገለፀው፡፡
የተመዘገበው ውጤት ዘላቂ እንዲሆን የመረጃ አያያዝ ሥርዓቱ መዘመን እንዳለበት የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴው በክልሉ የሚታየውን ሥራ አጥነት ለመቀነስ ፋይዳው የላቀ መሆኑ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል

Read More Âť
News

ብቁ የሰው ኃይል በስፋት በማፍራት የኢትዮጵያን ብልፅግና ዕውን የማድረግ ጉዞ

ብቁ የሰው ኃይል በስፋት በማፍራት የኢትዮጵያን ብልፅግና ዕውን የማድረግ ጉዞ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የአሰሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በተደራጀ መልኩ የሠለጠነ እና ብቃት ያለዉን የሰዉ ሃይል ለመንግስት ተቋማትና ለድርጅቶች ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ለሀገር ዉስጥ ሥራና ሠራተኛ ኤጀንሲዎችና ለሴክተር መዋቅር ፈጻሚዎች በብሔራዊ የሥራ ስምሪት ፖሊሲና ስትራቴጂ ፣ በአዲሱ የሥራና ክህሎት እሳቤ፣ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ፣ ደንብ እና መመሪያ ላይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በመድረኩ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮ ምክትል ሃላፊና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዮት ሸጋ በክልሉ ዉስጥ የሚገኙ አሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲዎች ለመንግስት ተቋማትና ለድርጅቶች የሚያቀርቡት የሰው ኃይል ብቁ፣ ተወዳዳሪና፣ በሥነ ምግባር የታነፀ እንዲሆን ለማስቻል ኤጀንሲዎቹ ኃላፊነታቸውን በሚገባ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡
ቢሮዉ አዲሱን የዘርፉን እሳቤ መሠረት ባደረገ መልኩ ዜጎችን በስልጠና የማብቃትና መዝኖ ብቃታቸውን የማረጋገጥ ሥራ እየሠራ እንደሚገኝ የክልሉ የሥራና ክህሎት ቢሮ ዘገባ ያመላክታል፡፡
ብቁ የሰው ኃይል በስፋት በማፍራት የኢትዮጵያን ብልፅግና ዕውን የማድረግ ራዕይን የሰነቀው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በማንኛውም የሥራ መስክ ላይ የሚሰማሩ ዜጎች መደበኛና መደበኛ ባልሆኑ ስልጠናዎች ራሳቸውን እንዲያበቁ፣ ተመዝነው ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል ሥርዓት ዘርግቷል፡፡
ሚኒስቴር መ/ቤቱ ሀገር ወዳድ፣ በሙያ ሥነ ምግባር የታነፀና በተሰማራበት መስክ ሁሉ ውጤታማ የሆነ ብቁ የሰው ኃይልን ለማፍራት የሚያስችል አዲስ የሪፎርም እሳቤን በመቅረፅም ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡

Read More Âť
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር …

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ማብቃትና ማሰማራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአቪዬሽን ዘርፍ የሰው ኃይል አቅርቦት፣ ስልጠና እና ስምሪት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ የኢትዮጵያ ወጣቶች በዘርፉ አሰልጥኖ ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁ አድርጎ ማቅረብ የሚያስችል ነው።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ እንደገለጹት፣ ስምምነቱ የከባተ ልምድ ያለውን የኢትዮጵያ የአየር መንገድ ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ በሌሎችም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለአቬሽን ዘርፉ ብቁ ወጣቶችን አሰልጥኖ ለሀገር ውስጥና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ በቀለ ባይ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ በዓመት ከ3 ሺህ እስከ 4 ሺህ የሚደርስ አዲስ ሠራተኛ እንደሚቀጥር ጠቁመዋል።
ሰራተኞችን የመመልመል እና የማሰልጠን ሂደት አድካሚና ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር መሥራት የሥራ ድግግሞሽን ከማስቀረቱም በላይ የሀገሪቱን ወጣቶች በአግባቡ በማብቃት ተወዳዳሪ ዜጎችን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ከኮቪድ-19 በኋላ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአቪዬሽን ባለሙያዎች እጥረት እንዳለ የገለጹት ኃላፊው ይህንን ክፍተት ለመሙላት በቂ እና ብቁ ወጣቶችን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በትብብር እና በቅንጅት ማሰልጥን ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ገልጸዋል፡፡
በዚህ ስልጠና የሚያልፉ ወጣቶች በዋናነት ለኢትያጵያ አየር መንገድና ለሌሎችም ሀገራት አቬየሽን የማቅረብ ሥራ በስፋት እንደሚሠራ ጠቁመዋል፡፡
ይህ ስምምነት የዜጎችን ሙያዊ ብቃት በማጎልበት በማሳደግ፣ በየትኛውም የዓለም ብቁ ተወዳዳሪ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲሰሩ ያስችላል ተብሏል፡፡
በቀጣይም የመግባቢያ ስምምነቱ ወደ ዝርዝር ዕቅድ ተቀይሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር እንደሚገባ ተገልጿል።

Read More Âť
News

ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል

ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል
የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ስትሪንግ ኮሚቴ ዕቅድ አፈፃፀሙን ክቡር አምባሳደር አምባሳደር ግርማ ብሩን ጨምሮ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገምግሟል፡፡
በዚህም ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎችን ጥራት ያለው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ በመድረኩ ተጠቁሟል፡፡
በመድረኩ ላይ እንደተመለከተው፣ የተመዘገበው ስኬት የሰው ኃይል ዝግጅትን፣ የሥራ ገበያ ፍላጎትንና ለሥራው ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርን ማዕከል ባደረገ የጋራ ዕቅድ ሁሉም ባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ተሰናስለው በመስራታቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ይህ የተቀናጀ አሠራር የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ባለፉት ሰባት ወራት በተተከናወኑ ሥራዎች የተገኘው ውጤት፤ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ መሻሻል የታየበት መሆኑ ተመላክቷል።
በቀጣይም በሰው ኃይል ዝግጅት ረገድ የግል ዘርፉና ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸው ድርጅቶች በስፋት እንዲሳተፉ ማበረታታት እንደሚገባ ተመላክቷል።
ይህም የዜጎችን ተወዳዳሪነትና የሥራ ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ መሆኑና የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎችን በላቀ ትጋት ማጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
somSOM
Scroll to Top