Mols.gov.et

News

News

በዚህ ዓመት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በአዲስ ምዕራፍ እና …

በዚህ ዓመት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በአዲስ ምዕራፍ እና በላቀ ግብ መተግበር መጀመራችን ይታወሳል፡፡
በዘርፉ የተቀመጠው የተለጠጠ ግብ ከማሳካት ባለፈ የዜጎች መብትና ደህንነትን ያስጠበቀ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸውን ያረጋገጠ እንዲሆን በጥብቅ የክትትልና ድጋፍ ሥራ እንዲመራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ በተገኙበት የአንድ ወር አፈፃፀማችንን ገምግመናል፡፡
በዚህም ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የአስፈፃሚ አካላት ዕቅድን የተናበበ ለማድረግ የተጀመረው ሥራን ማጠናከር እና የተሻለ የመቀበል አቅም ያላቸው መዳረሻ ሀገራት ላይ አተኮሮ መስራት እንደሚገባ ተመልክተናል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን የሀገር ውስጥ የሥራ ገበያውን ታሳቢ ያደረገ ስልጠናን ማጠናከር ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ መደላድል የሚፈጥር በመሆኑ አንዱ የርብርብ ማዕከል መሆን እንደሚገባው ተግባብተናል፡፡

Read More »
News

የ2016 ዓ.ም የሥራ ጉባኤ እና ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅትን…

“ጉባኤው አሠሪው፣ ሠራተኛና መንግስት በጋራ የሚመካከሩበት እና ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሰላም ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ የሚፈጠርበት ነው፡፡”
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚንስትር
የ2016 ዓ.ም የሥራ ጉባኤ እና ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅትን የተቀላቀለችበት መቶኛ ዓመት ክብረ በዓል አስመልክቶ ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የዓለም የሥራ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አሠሪዎች ፌዴሬሽን ኮንፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ የሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ከህዳር 24-26/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄደው ኮንፈረንስ አስመልክቶ የሥራና ክህሎት ሚንስትር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት ጉባኤው ስለ አሠሪው እና ሠራተኛው አብረን የምንመክርበት፣ የጎደለውን የምንሞላበት፣ ያለውን የምናጠናክርበት፣ እንዲሁም ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሰላም ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ የሚፈጠርበት ነው፡፡
ከዚህ ባለፈም ኮንፈረንሱ ከዓለም የሥራ ድርጅት ጋር ያለንን ትብብር የምናጠናክርበት፣ የመጣንበትን ርቀት የምንፈትሽበት፣ ስኬቶቻችንና ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች የምንፈታበት፣ ድሎቻችንን የምናከብርበት፣ በሂደቱ አዎንታዊ ሚና ሲጫወቱ የነበሩትን አካላት እውቅና የምንሰጥበት እና ለቀጣይ ጉዟችን ስንቅ የምንሰንቅበት ይሆናል ብለዋል፡፡
የዓለም ሥራ ድርጅት ካንትሪ ዳይሬክተር እና የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ተወካይ ክቡር አሌክስዮ ሙሲንዶ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት የዓለም ሥራ ድርጅትን በመቀላቀል ከቀዳሚዎቹ አንዷ መሆኗን ገልጸው የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ፣ ጾታዊ ትንኮሳ፣ ህገ-ወጥ ስደትን መከላከል የመሳሰሉት ተግባራት በድርጅቱ የወጡ ህጎች ወስዳ በመተግበር ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡
ጉባኤው ማህበራዊ ፍትህ በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ ይምንመክርበት እና በቀጣይ ስለምናከናውናቸው ተግባራት በጥልቀት የምንወያይበት እና አቅጣጫ የምናስቀምጥበት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
የጋዜጣዊ መግለጫን በጋራ የሰጡት የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አሠሪዎች ፌዴሬሽን ኮንፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ የሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የሥራ ኃላፊዎች በጉባኤው አሠሪና ሠራተኛ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳይቾ ጎልተው የሚወጡበት እና ምርታማነትን በሚያረጋግጡ ጎዳዮች ላይ መክረን የምንግባበት ይሆናል ብለዋል፡፡

Read More »
News

” የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘና እና ማረጋገጫ…

” የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘና እና ማረጋገጫ ሥርዓቱ የሥልጠና ጥራቱን ለማስጠበቅ ካለው ፋይዳ ባሻገር የዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡ “
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሙያ ብቃት ምዘና እና ማረጋገጫ ስርዓቱን ለማዘመን እየተከናወኑ ባሉ የሪፎርም ሥራዎችና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ከክልል የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አደረገ፡፡
በበይነ መረብ በተካሄደው በዚህ ውይይት ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻን ጨምሮ የሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳድሮች የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
በውይይቱ በቅርቡ በልጽጎ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስርዓት አተገባበር፣ የመደበኛና አጫጭር ስልጠና አጠናቃቂዎችን ብቃታቸውን በምዘና የማረጋገጥ አፈፃፀምና የገጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ክፍተት ምክንያት በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽዕኖ እና እሱን ለመቀነስ መወሰድ ስላለባቸው የእርምት እርምጃዎች ላይ ጥያቄዎች ተነስተው ማብረሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በውይይቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ በዘርፉ የሥልጠና ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም ሀገራዊ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስርዓቱ ወጥነት ያለውና በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስርዓት ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፡፡
ሥርዓቱ የሥልጠና ጥራቱን ለማስጠበቅ ካለው ፋይዳ ባሻገር በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት የሚያግዝና የዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ በሁሉም ክልል ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በበኩላቸው የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስርዓቱ በዘርፉ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት እንዲሰፍን እንድል የሚፈጥር ነው፡፡
ከዚህ ባለፈም ሀሰተኛ ማስረጃን መከላከል የሚያስችል እና በየዓመቱ ለሰርተፊኬት ህትመት የሚወጣውን ከፍተኛ በጀት የሚቀንስ ነው ብለዋል፡፡

Read More »
News

የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሙያ ማማከርና ድጋፍ አገልግሎት መምሪያ ሰነድ ይፋ ሆነ፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጀርመን ዓለም አቀፍ ትብብር (GIZ) GmbH፣ ካሪታስ ስዊዘርላንድ እና ከሌሎችም የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር ያዘጋጀው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የሙያ ማማከርና ድጋፍ አገልግሎት መምሪያ ይፋ ተደርጓል፡፡
መምሪያው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ አስፈፃሚ፣ ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት ይፋ የተደረገ የተደረገ ሲሆን ለሁሉም ክልሎችና ለሁለቱ ከተማ አስተዳድሮች የማስረከብ ሥራ ተከናውኗል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተወካይ ዶ/ር ተሾመ ለማ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ መምሪያው ሚኒስቴሩ በክህሎት ዘርፍ እየሰራው የሚገኘውን ሥራ የሚደግፍ፣ የክህሎት ሥልጠናውን የሚያሻሽል ብሎም የሰልጣኞችን እና ምሩቃን በመደበኛ ትምህርት ከሚያገኙት እውቀት በተጨማሪ ውስጣዊ አቅማቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ እና የሙያ የማማከር አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው፡፡
መምሪያው ወጣቶች የወደፊት የሥራ ዕድላቸው በሚያገኙት መረጃ ተመስርተው እንዲወስኑ የሚያግዝ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደየ ክልሎችና እና ከተማ አስተዳደሮች ነባራዊ ሁኔታ ውጤታማ የሚያደርግ አደረጃጀት በመፍጠር በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲሚገባ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡

Read More »
News

በውሀና ኢነርጂ ዘርፍ …

በውሀና ኢነርጂ ዘርፍ እንደ ሀገር ያሉንን ፀጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስምምነት ከውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር ተፈራርመናል።
ስምምነቱ በሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ልማት እንዲሁም ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ በጋራ መስራት የሚያስችል ሲሆን በተለይ “ግድቤን በደጄ” በተሰኘው መርሃ ግብር ለዜጐች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያልቅና ቴክኖሎጂውን ለማላመድና ለማሸጋገር የሚያስችል ነው።
የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋና የሥራ ባልደረቦቻቸው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማላቅ በጋራ ለመስራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ አክብሮትና ምስጋናዬ ይድረሳቸው።

Read More »
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር 20ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር አከበረ

”ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፣ በህብረት እንታገል” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተከበረ የሚገኘው የዓለም የጸረ ሙስና ቀን የፌደራል የፀረ ሙስና ኮሚሽን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማቱ በጋራ አክብረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አሰግድ ጌታቸው በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ጥቂቶችን በጊዚያዊነት የሚጠቅም ብዙሃኑንና ሀገርን በዘለቂነት የሚጎዳ ጸያፍ ተግባር በመሆኑ የተባበረ የፀረ-ሙስና ትግል ማድረግን ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ሙስና የሰው ልጆችን የማስተዋልና የጥበብ ምንጭ የሚያደርቅ ጣፋጭ መርዝ ነው ያሉት ክቡር ዶ/ር አሰግድ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማቱ አመራርና ሠራተኞች ጉዳቱን የሚመጥን ትግል ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡
የፌዴራል የፀረ-ሙስና ከሚሽን ም/ል ኮሚሽነር አቶ እሸቴ አስፋው በበኩላችን፤ የዘንድሮ የሙስና ቀን ስናከብር በተልዕኮ እና በተግባር እንዲሆን በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት አመራሩ ሀብቱ እንዲያስመዘግብ ከማድረግ ጀምሮ ተጨባጭ ሥራዎች እየተሰሩ እየተከበረ ነው፡፡
ሙስና ለሀገር ስጋት መሆን ስለታመነበት በሀገር አቀፍ ደረጃ የፀረ ሙስና ትግል ግብረ-ሀይል በማቋቋም የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በመድረኩ የሙስና መከላከል እና የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡

Read More »
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሴቶች ፎረም መደበኛ ሥብሰባ ተካሄደ

ሴት ሠራተኞች ያላቸውን እውቀትና ብቃት በጋራ በማቀናጀት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ የማስቻል ዓላማን በመያዝ ነበር የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሴት ሠራተኞች ፎረም ህዳር/2015 ዓ.ም የተመሰረተው፡፡
ፎረሙ ከምስረታው ጀምሮ እያከናወናቸው በሚገኙ ተግባራትና በቀጣይ በያዛቸው ዕቅዶች ላይ የሚመክር መደበኛ ስብሰባ አካሄዷል፡፡
በስብሰባው መክፈቻ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት የሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መከለያ በርጌቾ ፎረሙ ሴቶች እርስበእርስ የሚማማሩበት፣ የሚመካከሩበት፣ ሃሳብና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት መድረክ ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ አደረጃጀቱን ተጠቅሞ ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
መሰባሰብና መደራጀት ወደ መብቃት የሚወስድ አንድ አቅም ነው በማለት የገለፁት ወ/ሮ መከለያ በቀጣይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ አገር አቀፍ የሴቶች ፎረም ለመመስረት በሚኒስቴር መ/ቤቱ ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል፡፡
ፎረሙ ሴቶችን በማብቃት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት የሚያስችል አቅምን የመፍጠር ዓላማ ያለው መሆኑን የገለፁት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እርቅነሽ ዮሃንስ አዳዲስና ጉልበታም የሆኑ ሃሳቦችን በማዋጣት ፎረሙን የማጠናከር ሥራ ከሁሉም አባላት የሚጠበቅ ነው ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በመድረኩ ‹‹የራስን ሀብት መፈለግ›› በሚል ርዕስ ዕምቅ አቅምን በመፈተሸና በመጠቀም ላይ ያተኮረ ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በፎረሙ ዕቅድ አፈፃፀምና ቀጣይ እቅዶችም ላይም ውይይት ተደርጓል፡፡

Read More »
News

“ትብብሩ ከክህሎት ልማቱ ባለፈ የሁለቱን ሀገራት የረዥም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድግ ነው፡፡” ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

የቻይናው የትምህርት ቴክኖሎጂ ኩባንያ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በትብብር መስራት እንደሚፈልግ አስታወቀ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የድርጅቱን መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
በዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ላይ እያከናወናቸው ስላለው ተግባራት እና ሀገራዊ የልማት አቅጣጫዎችን አስረድተዋል፡፡
የቤጂንግ ዌዋ የመስመር ላይ (Online) የትምህርት ቴክኖሎጂ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ጃሰን ጂን በውይይቱ ላይ እንደገለጹት፣ ድርጅታቸው ለትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሥራውን የሚያቀሉ ዲጂታል የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን እንደሚያቀርብና በክህሎት ልማቱ ዘርፍ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በትብብር መስራት እንደሚፈልግ ገልፀዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመን የሚጠይቅ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ጃሰን ጂን በቴክኖሎጂ፣ በግብርና እና መሰል የሥልጠና ዘርፎች ዘመኑን የዋጁ ‹‹ሲሙሌተሮችን›› በመጠቀም ደረጃውንና ጥራቱን የጠበቀ ሥልጠና መስጠት ያስችላል ብለዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በትብብር ለመስራት ያለውን ፍላጎት አድንቀው ይህም ከክህሎት ልማቱ ባለፈ የሁለቱን ሀገራት የረዥም ጊዜ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድግ ነው ብለዋል፡፡

Read More »
News

” ተልዕኳችን ክህሎትን የማሰቢያ፣ የመወዳደሪያ እና የኢንቨስትመንት መሳቢያ መንገድ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስብራረቶቻችን ማከም የሚያስችል ነው፡፡”

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም የግምገማና የምክክር መድረክ የዘርፉ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት በተገኙነት ማካሄድ ጀምሯል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ዘርፉ እንደ ሀገር ያሉንን ተግዳሮቶች በመፍታት ያሉንን የመልማት ፀጋዎች አሟጦ ለመጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎችን የመፍጠር ወሳኝና የማይተካ ሚና ይጫወታል፡፡
ይህን ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ለማሳካት በተለመደው መንገድ ሄደን ልናሳካው ስለማንችል ባለፉት ሁለት ዓመታት “እየሰራን እየተደራጀን፤ እየተደራጀን እየሰራን” በሚል በመሪ ሀሳብ ለተልዕኮ ግብ ስኬት ዘርፎቹን በአዲስ እሳቤ በመምራት መደላድል ለመፍጠር ተሞክሯል፡፡
የክህሎት ልማት ዘርፉ ገበያ መር የሆነ የሥልጠና ሥርዓት በመከተል ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ የሆነ በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ ብቁና በቂ የሰው ኃይል ለማቅረብ ርብርብ ይጠበቃል፡፡
የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ የማዕክሮ ኢኮኖሚው ህመም ከሆኑ ጉዳየች መካከል አንዱ የሆነውን የሥራ አጥነት ችግርን ለመፍታት ያስችላል፡፡
የአሰሪና ሠራተኛ ግንኙነት ጤናማ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ በትብብርና በመግባባት ላይ የተመሰረተ እንዲሆንና ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻልና ለማረጋገጠ ወሳኝ ሚና አለው፡፡
ስለሆነም” ተልዕኳችን ክህሎትን የማሰቢያ፣ የመወዳደሪያ እና የኢንቨስትመንት መሳቢያ መንገድ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስብራረቶቻችን ማከም የሚያስችል ነው፡፡” ብለዋል፡፡
ይህም የአሁን ፍላጎታችንን ብቻ ሳሆን የዞሩ ድምሮቻችንንና የቀጣዩን ፍላጎት ከግምት ያስገባ እንቅስቃሴና ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅም አላክተዋል፡፡
መድረኩ እነዚህን ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳና ትርጉም ያላቸውን ተልዕኮዎች ከዳር ለማድረስ ትክክለኛ ቁመና ላይ መሆናችንን የሚፈተሸበት ጊዜ መሆኑን ያነሱት ክብርት ሚኒስትር በቀጣይ ጊዜያት ተጨማሪ አቅምና ጉልበት የሚፈጥሩ ተሞክሮና አሰራሮችን የምናይበት ነው ሲሉ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በግምገማና በምክክር መድረኩ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳድሮች የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት፣ የተጠሪ ተቋማትና የባለድርሻ አካላት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን መድረኩ ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል፡፡

Read More »
News

በሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የለሙ አዳዲስ ሲስተሞችን አስመልክቶ

በሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የለሙ አዳዲስ ሲስተሞችን አስመልክቶ ለክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ አመራሮች ገለጻ ተደርጓል፡፡
በቅርቡ ይፋ የተደረጉ ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው፤ ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበትና የሚሸጡበት ሉሲ የተሰኘ ሥርዓት፣ የድርጅቶች የተሟላ የሰራተኛ መረጃ መስጠት የሚያስችል ብቁ የሰራተኛ መመዝገቢያ ሥርዓት እና የተቀናጀ የሙያ ብቃት ምዘና ስርዓትን አስመልክቶ ገለፃና ማብራርያ ተሰጥቷል፡፡
ማብራርያውን የሰጡት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ እንደገለጹት የለሙት ሥርዓቶች ተግዳሮችን የሚፈቱና አሰራሮችን የሚያዘምኑ ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አማካኝነት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝድ ተደርጎ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+

The Ministry of Labor & Skills