Mols.gov.et

News

News

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ካውንስል ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ በተገኙበት መደበኛ ውይይቱን አካሂዷል፡፡

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ካውንስል ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ በተገኙበት መደበኛ ውይይቱን አካሂዷል፡፡
በመድረኩ ያለፉት ሁለት ወራትን ጨምሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ተመልክተናል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዕቅድንም በዝርዝር ተመልክተን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለይተናል፡፡
እያጠናቀቅን ባለው በጀት ዓመት የሥራ ስምሪቱን በቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የመዳረሻ ሀገራትን በማስፋት እና ከባለድርሻና ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር ተቀናጅቶ በመስራት የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሰፊ ጥረት ተደርጓል፡፡
በዚህም ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ አፈፃፀሙ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ45.8 በመቶ እድገት ያለው ቢሆንም ከያዝነው ግብ እና ዘርፉ ካለው እምቅ አቅም አኳያ ብዙ መስራት እንደሚገባን ተመልክተናል፡፡
በመሆኑም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫችን የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ላይ አተኩሮ የሰለጠነ የሰው ኃይል አቅርቦቱ የሥራ ገበያው ፍላጎቱን በአግባቡ ለመመለስ፤ የአገልግሎት አሰጣጡም ይህንኑ የሚያሳላጥ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላትና የዘርፉ ተዋንያን በተሰናለሰ አግባብ መስራት እንደሚገባን ተግባብተናል፡፡
ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ እየሰጡ ላለው ውጤታማና ጠንካራ አመራር እንዲሁም ሚናችሁን እየተወጣችሁ ላላችሁ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ!
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

Read More »
News

⚠️ለጥንቃቄ ⚠️

⚠️ለጥንቃቄ ⚠️
✅ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለዜጎች ምቹ፣ ዘላቂና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም በሀገር ውስጥ፣ በውጭ ሀገር እና በርቀት የሥራ ዕድሎች ያሉ አማራጮችን ሁሉ አሟጦ ለመጠቀም ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ተጨባጭና ተስፋ ሰጪ ውጤቶችም ተገኝተውበታል፡፡
🚨ከአሳሳች ማስታወቂያዎች ራስዎን ይጠብቁ❗️
✅ህገወጦች 🇨🇦ካናዳና 🇪🇺አውሮፓን ጨምሮ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት እንልካለን የሚሉ አሳሳች ማስታወቂያዎችን እያሰራጩ ይገኛል፡፡ ይህም ዜጎችንን ላልተገባ እንግልትና ወጪ እንዲሁም ለህገወጥ የሰዎች ዝውውር የሚዳርግና ህይወትዎን ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ነው፡፡
✅እርስዎም በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን ፍላጎቱ ካልዎት ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲሁም ለከፋ አደጋ ከሚዳርግዎ ህገ-ወጥ ዝውውር እራስዎን እንዲጠብቁ እየገለጽን የሚከተሉትን መረጃዎች ልብ እንዲሉ እናሳስባለን!
🌍 የሁለትዮሽ ስምምነት የተገባባቸው ሀገራት የትኞቹ ናቸው ❓
✅ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአሁን ወቅት ህጋዊ የሥራ ስምሪት እየሰጠባቸው የሚገኙ ሀገራት የሚከተሉት ሀገራት ናቸው፡-
1️⃣ሳዑዲ አረቢያ🇸🇦
2️⃣የተባበሩት አረብ ኤሚሬት🇦🇪
3️⃣ሊባኖስ🇱🇧
4️⃣ኳታር🇶🇦 እና
5️⃣ኩዌት🇰🇼 ናቸው፡፡
📢ልብ ይበሉ❗️
❌ ከላይ ከተጠቀሱት ሀገራት ውጪ ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሚሰጥባቸው ሀገራት የሉም፡፡
✍️ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን👇
📚 የውጭ ሀገር ሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (lmis.gov.et) በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ መሆን ይችላል፡፡
📚ከዚህ ባለፈ ወቅታዊና በቂ መረጃ ይኑርዎ! ለዚህም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ይፋዊ ድረ-ገጽን፣ የማህበራዊ ትስስር ገጽን፣ የብሔራዊ መገናኛ ብዙሃንን እና ተዓማኒነት ያላቸው ሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን እንደ መረጃ ምንጭነት ይጠቀሙ፡፡ አልያም አቅራቢያዎ በሚገኙ የክልል፣ የከተማ አስተዳደርና በየደረጃው ያሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መዋቅሮች በመገኘት መረጃ ማግኘት ይችላሉ!
🛑 አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥሞ በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የህግ አስከባሪ አካላትና በየደረጃው ለሚገኝ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መዋቅር ያሳውቁ❗️
📢 ይህን መልዕክት ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ♻️
✅ ሌሎችም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይጋለጡ ያድርጉ❗️

Read More »
News

ተጠናክሮ የቀጠለው የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና

ተጠናክሮ የቀጠለው የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የኮዲንግ ስልጠና በትኩረት እየሰጡ ይገኛል፡፡ በዚህም በርካታ ዜጎች አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡
የኮዲንግ ስልጠናው በትኩረት እየተሰጠ ከሚገኝባቸው ክልሎች አንዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ይገኝበታል፡፡
በአሁን ወቅት 4 ሺህ የሚጠጉ ዜጎች በክልሉ በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የኮዲንግ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛል፡፡ ከነዚህ መካከል በርካታዎች ስልጠናቸውን አጠናቀው የሰርተፍኬት ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡
በክልሉ የኮዲንግ ስልጠና በትኩረት በመስጠት ጥሩ አፈጻጸም እያስመዘገቡ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የወራቤ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተጠቃሽ ነው፡፡
ኮሌጁ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና አፈፃፁሙን በአሁን ወቅት 94 በመቶ ማድረሱን የኮሌጁ ዲን አቶ ቡላድ ናሙዝ ገልፀዋል፡፡
ኮሌጁ በቅድሚያ አሰልጣኝ መምህራን የኮዲንግ ስልጠናውን እንዲወስዱ በማድረግ የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆን ያደረገ ሲሆን 593 ሰልጣኞች ስልጠናውን በማጠናቀቅ የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆኑ አድርጓል፡፡
በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከታቀደው 740 የኢትዮኮደርስ ሰልጣኞች እስከ ግንቦት 30/2017 ድረስ 696 ሰልጣኞች የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ የኮሌጁን የኢትዮ ኮደርስ አፈፃፀም 94% ማሳካት መቻሉን ከክልሉ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Read More »
News

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ ባካሄደው ጉባኤ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል።
ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
በማብራሪያቸውም ረቂቅ አዋጁ ኢኖቬሽን ነባር አሠራሮችን፣ የምርትና የአገልግሎት ሂደቶችንና ምርቶችን በሳይንሳዊ መንገድ በመቀየር ሰዎች ሕይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሀገራት ይህን ከባቢያዊ ሥርዓት ለመፍጠር የሚያስችሉ ሕጎች ማውጣታቸውን እና በዚህ ዘርፍ ከተሰማሩ ከሃሳብ አፍላቂዎች ጀምሮ መዋዕለ ንዋያቸውን ኢንቨስት ላደረጉና ለሚያደርጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች የአገራቱ አቅም የሚፈቅደውን እና ተገቢ ነው ያሉትን የማበረታቻ ማዕቀፍ አዘጋጅተው ወደ ሥራ ማስገባታቸውንም አብራርተዋል፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ ይህን ሥርዓት መፍጠር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂን ከማስረጽና በኢኮኖሚው ውስጥ ሊያመጣ የሚችለውን አዎንታዊ ውጤት የሚመጣ፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅሙም ከፍተኛ የሆነ እንዲሁም በአገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ለውጥ ታሳቢ በማድረግ የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ነው የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) የገለጹት።
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ሀሳብን ወደ ገንዘብ የሚቀየርበትን መንገድ የሚፈጥር እና ፈጠራን የሚያበረታታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በስፋት ከተወያየበት በኋላ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 2320/2017 ሆኖ ለዝርዝር ዕይታ ለሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መምራቱን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Read More »
News

የአጋርፋ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ ያሰለጠናቸውን 897 የቀበሌ የልማት ጣቢያ ሰልጣኞች አሰመረቀ።

የአጋርፋ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ ያሰለጠናቸውን 897 የቀበሌ የልማት ጣቢያ ሰልጣኞች አሰመረቀ።
ለ13ኛ ጊዜ በተካሄደው የምረቃ ስነ-ስርዓት 624 የሚሆኑት ተመራቂዎች በእፅዋትና እንስሳት ሳይንስ፣ በተፈጥሮ ሀብትና በገጠር መሬት አስተዳደር እንዲሁም በአነስተኛ መስኖ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በደረጃ አራት የሰለጠኑ ናቸው፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕት፣ ተመራቂዎች በንድፈ ሀሳብና በተግባር ያገኙትን እውቀትና ክህሎት መሬት በማውረድ ግብርናውን ማዘመን እና ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል ይጠበቅባቹኋል ብለዋል፡፡
ስልጠናው የመጀመሪያቸው እንጂ የመጨረሻቸው አለመሆኑን አውስተው ተመራቂዎች በርትተው ለተጨማሪ እውቀት እራሳችውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን አቶ ፊራኦል ኤደኦ በበኩላቸው፤ ሰልጣኞች በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ታንፀው ከሥራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት ከመሸጋገር አልፈው ስሀገርን በመገንባቱ ረገድ ትልቅ ሚና መጨወት አለባቸው ብለዋል፡፡

Read More »
News

ለህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት

ለህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተግባራዊ እያደረገ ያለው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መነሻና መዳረሻው የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው፡፡
በዘርፉ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተሠራው ጠንካራ የሪፎርም ሥራ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ ወጪና እንግልት በመታደግ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህ ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እየቀጠለ ይገኛል፡፡
ነገር ግን ስምሪቱን በተመለከተ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ስምና አርማ እንዲሁም የከፍተኛ አመራሩን ስምና ፎቶ ጭምር በመጠቀም የተለያዩ ማስታወቂያዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሕገወጦች በመዘዋወር ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መሆናቸው ታውቆ ሁሉም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይዳረግ ጥንቃቄ እንዲያደረግ እናሳስባለን፡፡
የሥራ ስምሪቱን በተመለከተ አዳዲስ ነገሮች ሲኖሩ የተቋማችንን ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስርን ጨምሮ በሁሉም የሚደያ አማራጮች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልግ ማንኛው ሰው በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ ( elmis.gov.et ) እንዲመዘገብ እና ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

Read More »
News

በውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተጠናከረ ሁሉን አቀፍ ትብብር ያስፈልጋል። ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

በውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተጠናከረ ሁሉን አቀፍ ትብብር ያስፈልጋል።
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እያከናወናቸው በሚገኙ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች ለውጥ ካስመዘገባበቸው ዘርፎች መካከል የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት አንዱ ነው፡፡
ሚኒስቴር መ/ቤቱ በራሱ አቅም ባለማው ‹‹የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ ሥርዓት›› አማካኝነት ስምሪቱን ሙሉ ለሙሉ ዲጂታል ማድረግ መቻሉ ከዚህ በፊት በዘርፉ ይገጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ሁነኛ መፍትሄ መሆን ችሏል፡፡
በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት የሚያስችሉ ውይይቶችንና ምክክሮችንም በዘርፉ ከተሰማሩ የውጭ ሀገር አሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ጋር በተደጋጋሚ እያደረገ ይገኛል፡፡
በዚሁ መሰረት ኤጀንሲዎቹ ያላቸውን ብቃት በማሳደግ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚስችላቸው ሥልጠና ተጠሪነቱ ለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሆነው የኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢኒስቲትዩት ተሰጥቷል፡፡
ኢትዮጵያ በዓለም የሥራ ገበያ ውስጥ ያላትን ሚና ማሳደግ ለሁለት ቀናት የቆየው ስልጠና ዋንኛ ዓላማ ነበር፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በዘርፉ ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተጠናከረ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት አሳስበዋል፡፡
የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢኒስትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው የውጭ ሀገር አሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ጤናማ ካልሆነ ውድድር ተላቀው ፈጠራን ማዕከል ባደረገና ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን በጠበቀ መልኩ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚኖርባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኤጀንሲዎችና በመንግስት መካከል ጠንካራ ትብብር መፍጠር ዘላቂ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳ የሆነ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሥርዓትን በሀገራችን ለመተግበር ወሳኝ እርምጃ መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል፡፡

Read More »
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለተሰማሩና ከተለያዩ ኤጀንሲዎች ለተውጣጡ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለተሰማሩና ከተለያዩ ኤጀንሲዎች ለተውጣጡ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ አገር ሥራ ስምሪት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አርሚያስ ተክሉ እንደገለጹት፣ የዘርፉን አገልግሎት ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ በቴክኖሎጂ የማዘመንና አውቶሜት የማድረግ ሥራ ተሠርቷል።
ይህ በመሆኑም ኤጀንሲዎችም ሆኑ ተገልጋዮች ጉዳይ ለማስፈጽም ወደ ቢሮ መምጣት አንዳይጠበቅባቸውና አገልግሎቱም ካሉበት እንዲያገኙ ዕድል ፈጥሯል።
ይህ ስልጠና በዘርፉ የተሰማሩ ኤጀንሲዎች ስርዓቱን በአግባቡ ተገንዝበው በመጠቅም ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ አውቶሜት መደረጉን የጠቆሙት አቶ ኤርሚያስ ከዚህ በኋላ ለተለየ ኬዝ በኦን ላን በልዩ ሁኔታ ቀጠሮ አስይዘው ካልሆነ በስተቀር ተገልጋዮች ወደ ቢሮ መምጣት እንደማያስፈልጋቸው አመላክተዋል።
በስልጠናው ከአንድ ሽህ በላይ የሚሆኑና ከተለያዩ ኤጀንሲዎች የተውጣጡ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች ተሣትፈዋል።

Read More »
News

ለውጭ ሀገር የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ….

ለውጭ ሀገር የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች አዲስ የሥራ ፈቃድ ፣ የእድሳት፣ የክሊራንስና የጠፋና የተበላሸ ሥራ ፈቃድ ምትክ አገልግሎት በሥራ ገበያ መረጃ ድረገፅ www.lmis.gov.et አማካኝነት በቀጥታ እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
አሁን ደግሞ ተጠቃሚዎች የአገልግሎት ክፍያቸውን በቴሌብር አማካኝነት መፈፀም፣ የሚላክላቸውን IMV ቁጥር ተጠቅመው የሥራ ፈቃዳቸውን በድረ ገፁ ላይ ማግኘትና ወደ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መ/ቤት መምጣት ሳይጠበቅባቸው አትመው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ከዚህም በተጨማሪ አገልግሎቱን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በኩል ማግኘት እንደሚችሉም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
For All Foreign Work Permit Applicants
The Ministry of Labor and Skills now provides all foreign work permit services—including new applications, renewals, clearances, and replacements—online via www.lmis.gov.et.
Applicants can pay service fees through Telebirr, use the provided IMV number, and print their permits directly from the website—eliminating the need to visit the Ministry in person.
Services are also available at the Mesob One-Stop Service Center.
Ministry of Labor and Skills

Read More »
News

እያንዳንዱ የሥራና የምርት ሂደት የሚፈጥረውን የሥራ ዕድል አሟጦ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

እያንዳንዱ የሥራና የምርት ሂደት የሚፈጥረውን የሥራ ዕድል አሟጦ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ስለ ኢትዮጵያ የፓናል ውይይት “ሥራ ዕድል ፈጠራ ስለ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሀብቶች ያላት ሀገር ናት፡፡
ይህን ሀብት ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶችን በአግባቡ የለየ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ ተነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ወጤቶች መታየት ጀምሯል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ካላት ሀብት ትልቁ የሰው ሃይል መሆኑን ያነሱት ክብርት ሚኒስትር ይህንን ሀብት በአግባቡ አልምቶ ለመጠቀም በትኩረት እየተሰራ እንደሆነም አመላክተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከክህሎት ልማት፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትን አኳያ የቀረፃቸው የሪፎርም ሀሳቦችም የሰው ሃይላችንን ጨምሮ ያሉንን ፀጋዎች በመጠቀም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተነደፈውን ሀገራዊ ትልም ማሳካት የሚያስችል እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ የሥራ ዕድል ፈጠራ የዕለት ጉርን ከማግኘትና ዕለታዊ ችግሮችን ከመቅረፍ ባሻገር ሀብት መፍጠር ላይ የሚያተኩር፣ ጥራት ያለውና ዘላቂ ሥራ እንዲሆን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡
ለዚህም የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎት መርና እሴት ሰንሰለትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን መደረጉንም ነው ክብርት ሚኒስትር የገለፁት፡፡
አሁን ላይ የኢንተርፕራይ ምስረታ ሥራውም የሥራ እሴት ሰንሰለትን የተከተለ እዲሆን እንደተደረገም አንስተዋል፡፡
ይሄም በሥራ ሂደት፣ በምርት፣ በግብይት ስልት እና ስርዓት ላይ አዳዲስ ነገሮችን መጨመርን እና ለበርካታ ዜጎች ዘላቂና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል መፍጠርን ታሳቢ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል፡፡
ክህሎት መር እና እሴት ሰንሰለትን መሰረት ባደረገው የሥራ ዕድል ፈጠራ በቀላሉ የማይከስሙና ዘላቂና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ ኢንተርፕራይዞችን መፍጠር ያስችላል ሲሉም በአጽኖት አንስተዋል፡፡
እሴት ሰንሰለትን መሰረት ባረደገው የሥራ ዕድል ፈጠራ እያንዳንዱ የሥራ እና የምርት ሂደት የሚፈጥረውን የሥራ ዕድል አሟጦ መጠቀም እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
የሥራ ዕድል ፈጠራ ለብቻው የሚታይ ሳይሆን ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ጋር አሳተሳስሮ የሚተገበር እንደሆነ በየደረጃው በአግባቡ ግንዛቤ ሊያዝበት እንደሚገባም ነው ክብርት ሚኒስትር ያሳሰቡት፡፡

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top