
ብሩህ ተስፋ…
ብሩህ ተስፋ…
በሀገራችን በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን የክህሎት ባንክ ወደ ሥራ አስገብተናል፡፡
ባንኩ እንደ ሀገር ያለንን ዕምቅ የልማት ፀጋዎች አሟጦ በመጠቀም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር ያለንን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡
እንደ ዘርፍ እየተተገበሩ ከሚገኙ የሪፎርም አጀንዳዎች መካከል የሥራ ፈጠራ ስነ- ምህዳር ግንባታ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በዚህም ለፈጠራ ተሰጥኦና ፍላጎቱ ያላቸው ዜጎች ሀሳባቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበት መርሃ ግብሮች በየደረጃው ሲካሄዱ ቆይቷል፡፡
ቀደም ሲል ከወራት በፊት ዲጂታል የሥራ ሀሳብና የቴክኖሎጂ ባንክን በውስጥ አቅም አልምተን ተግባራዊ አድርገናል::የእነዚህ መሰረተ ልማት አቅሞች ችግር ፈቺና ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ ቴክኖሎጂዎች ብቻ ሳይሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ቴክኖሎጂዎችን መስራት የሚችሉ እውቀቱ፣ ክህሎቱና ብቃቱ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ያሉን መሆኑን ሂደቱ አረጋግጦልናል፡፡
ወደ ሥራ ያስገባነው የክህሎት ባንክም የሥራ ፈጠራ ሀሳብና ቴክኖሎጂዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ በየትምህርትና ስልጠና ተቋማቱ በሚገኙ ቤተ-መጽሀፍትና ወርክሾፖች ውስጥ የሚቀሩ ሳይሆኑ ወደ ተግባር ተቀይረውና ወደ ገበያ ገብተው የሀገርንና የዜጎችን ችግር በመፍታት እንዲሁም ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማሳካት የሚደረግውን ርብርብ የሚያግዙ ናቸው፡፡
በክህሎት ባንኩ ከሀሳብ ወደ ምርትነት የተቀየሩ በርካታ ቴክኖሎጂዎች ይገኛሉ፡፡ እያንዳንዱን ቴክኖሎጂ ወደ ብዝሃ ምርት (ማስፕሮዳክሽን) በማሸጋገር ለብዙዎች ተስፋ የሚሆኑ ስታርታፖችን፣ ዩኒ ኮርኖችን እና ካምፓኒዎችን ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም የሁሉንም ባለድርሻና አጋር አካላትን ሁሉን አቀፍ ርብርብ ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም ባንኩን በመጎብኘት ቴክኖሎጂዎቹ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እንዲሸጋገሩ የበኩላችሁን ሚና እንድትጫወቱ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡
የሪፎርም አጀንዳዎቻችን በተግባር እንዲገለፁ ላደረገው የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም የመጀመሪያው የሥራ ፈጠራ ሀሳብና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ እንዲሁም የክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር ተሳታፊዎች ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!