Mols.gov.et

News

News

የፈንላንድ የልማት ትብብርና የውጭ ንግድ ሚንስትር …

የፈንላንድ የልማት ትብብርና የውጭ ንግድ ሚንስትር ክቡር ቪሌ ታቪዮ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩትን ጎበኙ፡፡

በፊንላንድ የልማት ትብብርና የውጭ ንግድ ሚንስትር ክቡር ቪሌ ታቪዮ የተመራ የልዑካን ቡድን በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አካሂዷል፡፡ ልዑኩ የአውሮፓ ህብረት ተወካይ፣ በኢትዮጵያ የፊንላንድ አምባሳደር፣ እና ሌሎች አባላትን አካትቷል፡፡
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር ሚንስትሩን ተቀብለው የፊንላንድ መንግስትና ህዝብ ለኢንስቲትዩቱ እያደረጉ ያለውን ድጋፍ እና የወደ ፊት የትብብር ዕቅዳቸውን አቅርበዋል፡፡

ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ1960ዎቹ ጀምሮ በትምህርት፣ በግብርና፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ፣ በሌሎችም ዘርፈ ብዙ የልማት ትብብር ጉዳዮች አብረው ሲሰሩ መቆታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ ስልጠናን ዘመናዊ ለማድረግ የአሰልጣኞች የአቅም ግንባታ ስራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው (MOPEDE) ፕሮጀክት ባለፉት አራት ዓመታት ለኢንስቲትዩቱ የአይሲቲ መሰረተ-ልማት እያሟላ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ፕሮጀክቱ የአሰልጣኞች አቅም ግንባታ ላይ ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ በተጨማሪም ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ዘመናዊ ዲጂታል ስቱዲዮ ገንብቶ ማስረከቡን ገልጸዋል፡፡

ሚንስትሩ ቪሌ ታቪዮ በበኩለቸው በአገራቸው ድጋፍ የተሰሩ ዲጂታል ስቱዲዮዎችን፣ ስልጠና ያገኙ እና በዚህም ዲጂታል ኮንተንት እያዘጋጁ ያሉ አሰልጣኞችን ካዩ በኋላ አብረው መስራት በመቻላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በትምርትና ስልጠና ዲጂታይዜሽን አገራቸው የዳበረ ልምድ ያላት መሆኑት የጠቀሱት ሚንስትሩ የኢንስቲትዩቱ አሰልጣኞች አቅማቸውን በመገንባት ለኢንዱስትሪ አቅም የሚሆኑ ብቁ ሙያተኞችን ማፍራት እንዲችሉ አገራቸው አጠንክራ ትሰራለች ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የሥራ ድረጅት ምክትል የበላይ አካል (ILO governing body) ሆና ተመረጠች

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የሥራ ድረጅት ምክትል የበላይ አካል (ILO governing body) ሆና ተመረጠች
በጄኔቫ እየተካሄደ በሚገኘው 112ኛው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ኮንፈረንስ ላይ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሚመራ የልዑካን ቡድን በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
ጉባዔው ዛሬ ባከሄደው የዓለም ሥራ ድረጅትን በበላይነት የሚያስተዳድሩ ምክትል አባል ሀገራት መካከል ኢተዮጵያ አንዷ ሆና ተመረጣለች፡፡
ከአፍሪካ ከተወዳደሩት ሰባት ሀገራት መካከል ሀገራችን ኢትዮጵያ ከደቡብ አፈሪካ ቀጥላ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነው የተመረጠችው።
ደርጅቱን በበላይነት የሚያስተዳድሩ (governing body) አባል ሀገራት የዓለም ሥራ ድረጅት (የILO) ዋና ሥራ አሰፈፃሚ አካል ሲሆን የድርጅቱን ዋና ዳይረክተር ምርጫን ጨምሮ በድርጅቱ ፖሊሲዎች፤ ፕሮገራሞችንና በጀት ላይ ለሚቀጥሉት 3 አመታት የሚወስን አካል ነው፡፡
ይህም ሀገራችን በድርጅቱ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርጅቱን ሥራ በቅርብ ለመከታተልና ከድርጅቱ ተገቢውን ድጋፍ ለማግኘት ካለው ፋይዳ ባለፈ የአገራችንን ተደማጭነት በመጨመር የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውክልና ከፍ በማድረግ የገፅታ ግንባታችንን እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ደረጃችንን ያሳድጋል።

Read More Âť
News

ኢትዮጵያ በጄኔቫ እየተካሄደ ባለው 112ኛው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ኮንፈረንስ ላይ እየተሳተፈች ነው።

ኢትዮጵያ በጄኔቫ እየተካሄደ ባለው 112ኛው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ኮንፈረንስ ላይ እየተሳተፈች ነው።
በጄኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው 112ኛው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ኮንፈረንስ ላይ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሚመራ የልዑካን ቡድን በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
ሚኒስትር ዴኤታው በምልአተ ጉባኤው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህን ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት እንዲሁም በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተከናወኑ ሌሎች ተያያዥ የሪፎርም ሥራዎችን አንስተዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ተግባራዊ በማድረግ ላይ የምትገኘው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 እና ከዘላቂ ልማት ግቦች ጋር የሚጣጣም መሆኑን ጠቁመው አበረታች ውጤት እየተገኘ እንደሆነም አንስተዋል፡፡
በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ላይ ትልቅ ፋይዳ ያለውን የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓትን ጨምሮ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና የኢንዱስትሪ ሰላምን በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሻሻል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በመድረኩ ላይ ጠቁመዋል፡፡

Read More Âť
News

እሳቤዎቻችንን ለማጽናት…

እሳቤዎቻችንን ለማጽናት…

ባለፉት ሁለት ዓመታት ከክህሎት ልማት፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራ እና ከሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት አኳያ እንደ ተቋም የተሰጠንን ሀገራዊ ተልዕኮ ለማሳካት የሄድንበትን ርቀት ባለፉት 5 ቀናት ከዘርፉ አመራሮች ጋር በጋራ ገምግመናል፡፡

ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ከተጠሪ ተቋማት እና ከክልል የዘርፉ አመራሮች ጋር በነበረን በዚህ መድረክ እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ከተቋቋምን ጀምሮ የተከናወኑ ሥራዎችን በጥንካሬና በእጥረት ያሉትን ሥራዎች ለይተን የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠናል፡፡

በዚህም በሦስቱ ዘርፎች ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ እሳቤዎችና ቅንጅታዊ ሥራዎቻችን ፍሬ ማፍራት መጀመራቸውን እና የተቋም ግንባታ ሥራችንም ውጤታማ እንደነበር አይተናል፡፡ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና እጥረቶችን ለማረም በሚያስችል መልኩ መዘጋጀት እንዳለበት አንስተን ሂደቱም ፈጠራ የታከለበት ልዩ የአመራር ሥርዓትን የሚከተል፣ አስቻይ ሁኔታዎችን የሚፈጥር፣ ማነቆዎችን የሚፈታ እና አቅሞቻችንን ማብዛት ላይ የሚያተኩር መሆን እንደሚገባው ተግባብተናል፡፡

የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የሙያ ብቃት ምዘናና የአንድ ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን አገልግሎት አሰጣጥ የማዘመን እና ፈጠራ የታከለበትና ከፍተኛ የማደግ አለኝታ ያለቸውን ኢንተርፕራይዞች በልዩ ሁኔታ መደገፍ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የኢትጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ይዞ የመጣውን ዕድል አሟጦ መጠቀም እና ለሁሉም ሥራዎቻችን ስኬት መሰረት ሊሆን የሚችለውን ማህበረሰብ አቀፍ የምርታማነት ውይይትን በተቀመጠለት ስታንዳርድ መተግበር በየደረጃው የሚገኘው የዘርፉ አመራር ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ሥራ መሆኑን ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል ለዘርፉ አመራሮች ተናግረዋል ፡፡

Read More Âť
News

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር …

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ ለፈጠራ ሀሳብና ለምርምር ምቹ የሆነ የስራ ከባቢ እንዲፈጠር ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት በኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተከናወኑ የልማት ስራዎችና የኢኖቬሽን ውጤቶችንም ተመልክተዋል።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በወቅቱ እንደገለጹት፤ በኢንስቲትዩቱ ለፈጠራ ሀሳብ ማፍለቂያ እና ለምርምር ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል።
ኢንስቲትዩቱ ከሀገር የልማት ግብ አኳያ ብቁ ሙያተኞችን እያሰለጠነ እንዲሁም በፈጠራና በእውቀት የሚመራ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመፍጠር ላይ ነው ብለዋል።
በየዓመቱ 10ሺህ ተማሪዎችን እያሰለጠነ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩቱ፤ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂስቶች መፍለቂያ እየሆነ መምጣቱንም ጠቅሰዋል።
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው የሀገርን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያሳካ ብቁ የሰው ኃይል ስልጠና እና ምርምር ዋነኛ ትኩረታችን ነው ብለዋል።
በዚህም የኢትዮጵያን ግብርና፣ ጤና፣ ቱሪዝም፣ ግብርና፣ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ ኮንስትራክሽንና ሌሎችን ይበልጥ የሚያዘምኑ በርካታ ቴክኖሎጂ በኢንስቲትዩቱ መፈጠራቸውን ማንሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Read More Âť
News

የኢትዮጵያ ስታርትአፕ ሽልማት…

#አሁን
#HappeningNow
የኢትዮጵያ ስታርትአፕ ሽልማት በመካሄድ ላይ ነው። በመርሃ ግብሩ ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ አመራሮች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ አጋሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ግንቦት 26/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድረገጽ፡- https://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et

Read More Âť
News

የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል ተመሠረተ

የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል ተመሠረተ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በምስረታው መርሃ ግብር ላይ እንደተናገሩት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለሀገራዊ ልማት በመካከለኛ^^ና ዝቅተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
ተቋማቱ የክህሎትና የዕውቀት ሽግግር በማድረግ ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ተመሳሳይ ተልዕኮ ካላቸው ተቀማት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በተደራጀ መልኩ ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዘርፉን ማስተሳሰር የሚያስችል የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል “ብቁ መሪነት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ መመስረቱን ገልጸዋል፡፡
ካውንስሉ ተቋማቱ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡ እንዲሁም ስራቸውን ተናበው የሚሰሩበት ወጥ የሆነ የአደረጃጀት ስርዓት መገንባት የሚያስችላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
የአመራር ካውንስሉ ጥናትና ምርምር በማድረግ ልዩነት መፍጠር የሚችል የሰው ኃይል ማፍራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
ካውንስሉ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ገበያ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ከማፍራት አንጻር ከምንጊዜውም በላይ ፍጥነትን፣ ፈጠራን፣ ጥራትንና ብዛትን ማዕከል አድርጎ እንዲሰራ አሳስበዋል።
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ብሩክ ከድር በበኩላቸው በኢትዮጵያ ከ2ሺህ በላይ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በመንግሥትና በግል ባለቤትነት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ከእነዚህም መካከል ከ100 በላይ የሚሆኑት የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ኮሌጆቹ የበርካታ ወጣቶችን ክህሎት በማበልጸግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ስራ እያከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
የበለጸገ ክህሎት የማስጨበጥ ስራው በተለይ ወጣቶች ከራሳቸው ባለፈ ለሀገራቸው ኢኮኖሚ የማይተካ ሚና እንዲጫወቱ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

Read More Âť
News

በአፍሪካና በባህረ ሰላጤው ሀገራት መካከል ፍትሃዊ እና ቀልጣፋ የሠራተኞች እንቅስቃሴ እንዲኖር የሚያስችል ውይይት በኳታር ዶሃ ተካሄደ

በአፍሪካና በባህረ ሰላጤው ሀገራት መካከል ፍትሃዊ እና ቀልጣፋ የሠራተኞች እንቅስቃሴ እንዲኖር የሚያስችል ውይይት በኳታር ዶሃ ተካሄደ፡፡

ውይይቱ በአፍሪካና በባህረ ሰላጤው ሀገራት መካከል ፍትሃዊ እና ቀልጣፋ የሠራተኞች እንቅስቃሴን እውን ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤ ተሬሳ የተመራ ልዑካን ቡድን በ‹‹ዶሃ ውይይት›› ያደረገውን ተሳተፎ አጠናቆ ተመልሷል፡፡

በመድረኩ የሠራተኞች እንቅስቃሴን ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ ከማድረግ ባለፈ በላኪና ተቀባይ ሀገራት መካከል ፍትሃዊ የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታና የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አስተዳደር አስፈላጊነት ላይ ሰፊ ውይይት እንደተደረገ የልዑካን ቡድኑ አመላክተዋል፡፡

በኳታር ዶሃ የተካሄደው ይህ ውይይት በአፍሪካና በባህረ ሰላጤው ሀገራት መካከል ፍትሃዊ እና ቀልጣፋ የሠራተኞች እንቅስቃሴ እውን ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ነው የልዑካን ቡድኑ ያመላከቱት፡፡

በመድረኩ ዮርዳኖስ፣ ሊባኖስ፣ እና የባህረ ሰላጤው የትብብር ምክር ቤት አባል ሀገራት እና የአፍሪካ ሀገራትን ጨምሮ የ33 ሀገራት ተወካዮች እና ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፈውበታል፡፡

Read More Âť
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጣልያን ዓለም አቀፍ ትብብር ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚያደርገው

ተግባራዊ የሚደረገው ፕሮጀክት ማዕከላቱ የሚሰጡትን አገልግሎት ጥራት የማሻሻልና ተደራሽነታቸውን ማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቆመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጣልያን ዓለም አቀፍ ትብብር ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ተግባራዊ የሚያደርገው የሥራ ገበያ ትስስርና ድጋፍ ፕሮግራም ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
ፕሮጀክቱ በቡሬ፣ በቡልቡላ፣ በጅማ እና በይርጋዓለም የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ዙሪያ በሚገኙ 16 ከተሞች ላይ ለሚኖሩ ዜጎች የእሴት ሰንሰለትን መሰረት ያደረገ የሥራ ዕድል የመፍጠር ዓላማ ያለው ነው፡፡
በዚህም ፕሮጀክቱ ተግባራዊ የሚደረግባቸው የአማራ፣ የሲዳማና የኦሮሚያ ክልሎች ተወካዮችን ጨምሮ ሌሎችም የሚመለከታቸውን አካላት ያካተተው የስትሪንግ ኮሚቴ በፕሮጀክቱ ትግበራ ዙሪያ ውይይት አካሄዷል፡፡
ውይይቱን የመሩት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በሥራ ሥምሪት አገልግሎት ማዕከላት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ጥራት የማሻሻልና ተደራሽነታቸውን የማስፋፋት ሚና ያለው ነው፡፡
ፕሮጀክቱ የሥራ ሥምሪት አገልግሎት ማዕከላትን ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፣ ከአግሮ ፕሮሰሰኒግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ከግል ንግድ ድርጅቶች ጋር የሚያስተሳስር ነው ብለዋል፡፡
ስለሆነም ክልሎች መሰል ዓላማ ያላቸውን ፕሮጀክቶች አቀናጅተው በውጤታማነት መምራት እንደሚኖርባቸው ነው ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሳሰቡት፡፡
በውይይቱ ፕሮጀክቱ በሚተገበርባቸው አካባቢዎች ከኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ጋር በትሥሥር የሚሰሩ ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማጎልበት ፓርኮቹ በሚገኙባቸው አካባቢዎች 16 የሥራ ሥምሪት አገልግሎት(PES) ማዕከላትን የማደስ፣ በግብዓትና ሎጀሲቲክስ የማሟላትና የባለሙያዎችን አቅም የመገንባት እንዲሁም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓትን(LMIS) ተግባራዊ የሚደረግበትን ሁኔታ በዝርዝር ተመልክተዋል፡፡
የሥራ ገበያ ትስስርና ድጋፍ ፕሮግራሙ ከ11ሺ በላይ የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read More Âť
News

በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ዜጎች በዘላቂነት ለመደገፍ በሚደረገው ጥረት ሚኒሰቴሩ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ተገለጸ፡፡

በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ዜጎች በዘላቂነት ለመደገፍ በሚደረገው ጥረት ሚኒሰቴሩ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ተገለጸ፡፡
በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ በአማራ፣ በትግራይ፣ በአፋር እና በቤንሻጉል ጉምዝ ክልሎች በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ዜጎችን በዘላቂነት መደገፍ የሚያስችል የ43.5 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ የሚከናወኑ ተግባራት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት፤ በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ዜጎችን ለማቋቋም እና በዘላቂነት ለመደገፍ የሚደረጉ ጥረቶችን ለማገዝ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እና ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት ይሰራል።
ፕሮጀክቱ በዋናነት የዜጎችን ህይወት በዘላቂነት በሚያሻሽሉ በክህሎት ስልጠና፣ በግጭቱ ለተጎዱ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ብድር አቅርቦት፣ በውሃ ፣ በንፅህና አጠባበቅ አገልግሎቶች፣ በማህበራዊ ትስስር እና በመሳሰሉት ተግባራት ላይ አትኩሮ ይፈጻማል ተብሏል፡፡
ይህ ፕሮጀክት በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) መሪነት ከኢጣሊያ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (AICS)፣ ከጀርመን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጂአይዜድ)፣ ከዴንማርክ ቀይ መስቀል ከሚደገፈው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመተባበር ተግባራዊ እንደሚደረግም ተጠቁሟል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top