Mols.gov.et

News

News

ብሩህ ተስፋ…

ብሩህ ተስፋ…
በሀገራችን በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን የክህሎት ባንክ ወደ ሥራ አስገብተናል፡፡
ባንኩ እንደ ሀገር ያለንን ዕምቅ የልማት ፀጋዎች አሟጦ በመጠቀም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር ያለንን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡
እንደ ዘርፍ እየተተገበሩ ከሚገኙ የሪፎርም አጀንዳዎች መካከል የሥራ ፈጠራ ስነ- ምህዳር ግንባታ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በዚህም ለፈጠራ ተሰጥኦና ፍላጎቱ ያላቸው ዜጎች ሀሳባቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበት መርሃ ግብሮች በየደረጃው ሲካሄዱ ቆይቷል፡፡
ቀደም ሲል ከወራት በፊት ዲጂታል የሥራ ሀሳብና የቴክኖሎጂ ባንክን በውስጥ አቅም አልምተን ተግባራዊ አድርገናል::የእነዚህ መሰረተ ልማት አቅሞች ችግር ፈቺና ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ ቴክኖሎጂዎች ብቻ ሳይሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ቴክኖሎጂዎችን መስራት የሚችሉ እውቀቱ፣ ክህሎቱና ብቃቱ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ያሉን መሆኑን ሂደቱ አረጋግጦልናል፡፡
ወደ ሥራ ያስገባነው የክህሎት ባንክም የሥራ ፈጠራ ሀሳብና ቴክኖሎጂዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ በየትምህርትና ስልጠና ተቋማቱ በሚገኙ ቤተ-መጽሀፍትና ወርክሾፖች ውስጥ የሚቀሩ ሳይሆኑ ወደ ተግባር ተቀይረውና ወደ ገበያ ገብተው የሀገርንና የዜጎችን ችግር በመፍታት እንዲሁም ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማሳካት የሚደረግውን ርብርብ የሚያግዙ ናቸው፡፡
በክህሎት ባንኩ ከሀሳብ ወደ ምርትነት የተቀየሩ በርካታ ቴክኖሎጂዎች ይገኛሉ፡፡ እያንዳንዱን ቴክኖሎጂ ወደ ብዝሃ ምርት (ማስፕሮዳክሽን) በማሸጋገር ለብዙዎች ተስፋ የሚሆኑ ስታርታፖችን፣ ዩኒ ኮርኖችን እና ካምፓኒዎችን ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም የሁሉንም ባለድርሻና አጋር አካላትን ሁሉን አቀፍ ርብርብ ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም ባንኩን በመጎብኘት ቴክኖሎጂዎቹ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እንዲሸጋገሩ የበኩላችሁን ሚና እንድትጫወቱ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡
የሪፎርም አጀንዳዎቻችን በተግባር እንዲገለፁ ላደረገው የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም የመጀመሪያው የሥራ ፈጠራ ሀሳብና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ እንዲሁም የክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር ተሳታፊዎች ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

Read More »
News

በበጀት ዓመቱ የማጠቃለያ ምዕራፍ የክልሎች አቅም የማጠናከር ሥራ በትኩረት ይሠራል። ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዲኤታ

በበጀት ዓመቱ የማጠቃለያ ምዕራፍ የክልሎች አቅም የማጠናከር ሥራ በትኩረት ይሠራል።
ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዲኤታ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀሙን ገምግሟል፡፡
በግምገማው በዘጠኝ ወሩ ከውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትና ከኢንዱስትሪ ግንኙነትና የሥራ ሁኔታዎች ቁጥጥር አንፃር የተከናወኑ ዝርዝር ሥራዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የላቀ አፈፃፀም ለማስመዝገብ የተቀናጀና የተናበበ ሥራ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡
ከአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አንፃር የተያዙ ዕቅዶችን ከማሳካት አንፃር ከፍተኛ መሻሻሎች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው ዘርፉን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ የወሳኝ ቦርድ አደረጃጀትን በክልሎች ማስፋትና የሙያ ደህንነትና ጤንነትን ጉዳይ በሁሉም የሥራ ቦታዎች ሜይንስትሪም ማድረግ የሚያስችል ንቅናቄ መፍጠር የዘርፉ የቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሚሆኑ ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ የማጠቃለያ ምዕራፍ የክልሎችን አቅም የማጠናከር ሥራ በትኩረት እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡

Read More »
News

በቱሪዝም ሴክተሩ ካሉ አደረጃጀቶች ጋር በሰለጠነ የሰው ሃይል ልማትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ…

በቱሪዝም ሴክተሩ ካሉ አደረጃጀቶች ጋር በሰለጠነ የሰው ሃይል ልማትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችለንን ውጤታማ ውይይት አካሂደናል፡፡
በውይይቱ የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም አሰሪዎች ፌደሬሽን፣ የኢትዮጵያ ቱር ኦፐሬተርስ ማህበር፣ የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች ማህበር እና የታልቅ ኢትዮጵያ አስጎብኝዎች ማህበር ፕሬዝዳንቶች የተገኙ ሲሆን በመስኩ በትብብር መስራት የሚያስችሉንን ጉዳች ተመልክተናል፡፡
በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦትን ለማሻሸል፣ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ ትብብርና ቅንጅት ለማጠናከር እና እሴት ሰንሰለቱን መሰረት በማድረግ ጥራት ያለው የሥራ ዕድል መፍጠር የሚቻልበትን ሁኔታም በዝርዝር ተመልክተናል፡፡
መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ለኢኮኖሚው የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን አቅም አሟጦ ለመጠቀና አጠቃላይ ስነ-ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ ካለው ውስን ሀብት ወሳኝ የሆኑ መሰረተ ልማቶቹ እንዲሟሉ እያደረገ ይገኛ፡፡
ለዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል ፍላጎትም ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ ይገኛል፤ ይህንንም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ያሉ ማህበራት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበት የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም አሰሪዎች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት፣ ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች ማህበር ፕሬዝዳንት፣ አቶ ፍጹም ገዛኽኝ የኢትዮጵያ ቱር ኦፐሬተርስ ማህበር ፕሬዝዳንት እና አቶ ዳንኤል ተስፋየ የታልቅ ኢትዮጵያ አስጎብኝዎች ማህበት ፕሬዝዳንት በትብብር ለመስራት ላሳያችሁን ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

Read More »
News

“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት 3ኛ ዙር ስልጠና በድሬዳዋ …

የ2017 ዓ.ም “ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት 3ኛ ዙር ስልጠና በድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተጀመረ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት ከወረዳዎች የተመለመሉ ወጣቶች በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ስልጠና እየወሰዱ ነው::
ስልጠናው ለ12 ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይና ተሳታፊ የሚሆኑ ወጣቶች የህይወት ክህሎትና የሥራ ላይ ልምምድ ስልጠና እንደሚያገኙ ተጠቁሟል።
ሰልጣኞች ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ ኢንዱስትሪዎች ላይ ተመድበው የሥራ ላይ የተግባር ልምምድ የሚያደርጉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Read More »
News

የከተማችንን ፈጣን ዕድገት በሚመጥን መልኩ ዜጎች በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ

የከተማችንን ፈጣን ዕድገት በሚመጥን መልኩ ዜጎች በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው ።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት በሚመጥን መልኩ ዜጎች በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ አስታውቋል።
በተመረጡ ቦታዎች አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን በዶሮ ጥብስ ሥራ በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።
በዚህም ዜጎች “የኛ ዶሮ” በሚል ስያሜ በማህበር ተደራጅተው የተጠበሰ የዶሮ ውጤት ለገበያ እንዲያቀርቡ ለማድረግ ከመስሪያ ቦታ ዝግጅት ጀምሮ የመሸጫ ሱቆች ዲዛይን ሥራ እና ለማህበራቱ በሚሰጥ የብድር እና የመስሪያ ዕቃዎች አቅርቦት ላይ መክሯል።
በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስፋው ለገሰ፤ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ብሎም የኮሪደር ልማቱን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በተለያየ ዲዛይን አማራጭ እስከ አምስት ሰዎችን በማህበር በማደራጀት ምርቶቹ ለገበያ ለማቅረብ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ ባለ ድርሻ አካላት በበኩላቸው ለፕሮጀክቱ ስኬት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ያረጋገጡ ሲሆን በተሰጠው የዲዛይን አማራጭ መሰረት በማድረግ የመስሪያ ሱቆቹን ለመስራት ቃል እንደገቡ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Read More »
News

የገጠር የሥራ ዕድልን ለወጣቶች ሳቢ ለማድረግ የሚከወን ጥረት

የገጠር የሥራ ዕድልን ለወጣቶች ሳቢ ለማድረግ የሚከወን ጥረት
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሻሸመኔ ከተማ በኢንተርፕራይዝ ለተደራጁ ወጣቶች፣ አርሶ አደሮች፣ የኅብረት ሥራ ማኅበራትና ዩኒየኖች 1 ሺህ 402 የእርሻ ትራክተሮችን አስተላለፈ።
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ 576 አባላት አባላት ላላቸውና 105 ሚሊዮን ብር በላይ ለቆጠቡ 137 እንተርፕራይዞች ትራክተሮቹን አስረክበዋል፡፡
የትራክተሮቹ ድጋፍ በገጠር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ላይ ወጣቶችን በስፋት ተሳታፊ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዘውን ዕቅድ ከማሳካት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም መገለፁን የኦሮሚያ ሥራና ክህሎት ቢሮ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

Read More »
News

የዘመናት ጥያቄ ምላሽ…

የዘመናት ጥያቄ ምላሽ…
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የተደረገው የግብርና ልማት ባለሙያዎች የደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አስጀምረናል።
ከእጅ ወደ አፍ የነበረው የግብርና ዘርፍ መዋቅራዊ ለውጥ እንዲያመ ጣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል:: ለተመዘገበው እጅግ ተስፋ ሰጪ ውጤት የግብርና ልማት ባለሙያዎች ሚና የማይተካ ነበር።
ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮምቦልቻ ግብርና ኮሌጅ እና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አጋርፋ የግብርና ኮሌጅ በትብብር በሚካሄደው በዚህ የደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መርሃ ግብር የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እያካሄደ ካለው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም አጀንዳዎች መካከል ፍላጎት/ገበያ መር የስልጠና ስርዓት አንዱ ሲሆን የግብርና ዘርፉን ለማዘመን የተያዘውን ግብ ለማሳካት ጊዜውን በዋጀ ክህሎት የበቃ ሙያተኛ ፋይዳው የላቀ ነው።
ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ግንባር ቀደም ተሰላፊ የሆኑትን የግብርና ልማት ባለሙያዎች ህይወት ከማሻሻልም አንፃር ሚናው ከፍተኛ ነው።
የግብርና ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ግርማ አመንቴ ለበርካታ ዓመታት በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሱ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በሚፈታ መልኩ በቀጣይነትም ዘርፉ ጊዜውን በዋጀ እውቀት፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ እንዲመራ በትብብር ለመሥራት ለሰጡት ጠንካራ አመራር እንዲሁም ለመርሃ ግብሩ ስኬት በየደረጃው ርብርብ ስታደርጉ ለነበራችሁ የግብርና ሚ/ር እና የሥራና ክህሎት ከፍተኛ አመራርና ባለሙያዎች ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
የኮምቦልቻ አከባቢ ህዝብና የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ለተደረገልን ደማቅ አቀባበል አመስግናለሁ።

Read More »
News

በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረዉ አመታዊ የክህሎት ፣ የቴክኖሎጂ እና የተግባር ጥናትና ምርምር ዉድድር ተጠናቀቀ።

በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረዉ አመታዊ የክህሎት ፣ የቴክኖሎጂ እና የተግባር ጥናትና ምርምር ዉድድር ተጠናቀቀ።
ዉድድሩም በአሰልጣኝ፣ በሰልጣኝ ፣በአንቀሳቃሽ ኢንተርፕራይዞች መካከል በተለያዩ ዘርፎች ላይ እርስ በእርስ ልምድ የተወሰደበት ዉጤታማ ዉድድር እንደነበረም ተጠቁሟል።
የወልቂጤ ፖሊ ተክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሀይሩ አህመዲን እንዳሉት በወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች አመታዊ የክህሎት ፣ የቴክኖሎጂ እና የተግባር የጥናትና ምርምር በተካሄዱ ዉድድሮች መነሻ የሚያደርጉት በእያንዳንዱ ተቋማት ዉስጥ በአሰልጣኝ፣ በሰልጣኝ ፣በአንቀሳቃሽ ኢንተርፕራይዞች መካከል በተለያዩ ዘርፎች ላይ እርስ በእርስ የሚወዳደሩበት ዉድድር እንደሆነም አመላክተዋል።
በዚህ አመትም የክህሎት ልማቱ ያለበት ደረጃ ለማየት ፣ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ተመርተዉ ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸዉ የሚገመገምበት እንዲሁም ተቋማቶች ምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለመፈተሽ የሚደረግ ዉድድር እንደሆነም ተናግረዋል።
በክህሎት ፣ በቴክኖሎጂ እና በጥናትና ምርምር ዉድድሮች ሰልጣኝ ከሰልጣኝ ፣አሰልጣኝ ከአሰልጣኝ ፣ኢንተርፕራይዝ ከኢንተርፕራይዝ እንዲሁም ተቋም ከተቋም እየተወዳደሩ የሚፈተሽበት ዉድድር እንደሆነም አስታዉቀዋል።
በወልቂጤ ክላስተር ደረጃ 9 ኮሌጆች ፣ 25 ሰልጣኞች ፣ 47 አሰልጣኞች በክህሎት ዉድድር የተሳተፉበት ከ7 በላይ ኢንተርፕራይዞች በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተወዳደሩበትና እንዲሁም ከ20 በላይ ቴክኖሎጂዎች ቀርበዉ ዉድድር የተካሄደበት እንደነበረም ተገልጿል።
በቀጣይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ቢሮ በሚዘጋጀዉ ዉድድር ላይ ክላስተሩን ወክለዉ የሚወዳደሩ ሰልጣኞች አሰልጣኞች ፣ኢንተርፕራይዞች የተለየበት እንደሆነም ተነግሯል።
በዚህ ዉድድር አንዱ ተቋሙ ከሌላዉ ተቋም ልምድ የወሰደበት እንዲሁም ከባድ የሚመስሉ ስራዎችን እንዴት በጋራ መስራት እንደምንችል የታየበት መሆኑንም ተጠቁሟል።

Read More »
News

በአዲስ አባባ ሲካሄድ የነበረው የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ

በአዲስ አባባ ሲካሄድ የነበረው የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ15ኛው ቴክኒክና ሙያ ሳምንት አንዱ አካል የሆነው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር “ብሩህ አዕምሮዎች ፤ በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል በከተማዋ በሚገኙ ኮሌጆች በስድስት ክላስተር ተካሂዷል።
በቢሮው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ኢንኩቤሽን አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ በየነ እንደገለፁት፣ ውድድሩ በ19 የሙያ አይነቶች በ104 ሰልጣኞች መካከል ተካሂዷል።
የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ዕድገት በክህሎት በማዳበር እንዲሁም በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ የዘርፉን ዕድገት በማሳደግ ሂደት የክህሎት ውድድሩ ሚናው ጉልህ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በክላስተር የተካሄደው የክህሎት ውድድር መጠናቀቁን ተከትሎ የውድድሩ አሸናፊዎች በቀጣይ ከተማ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር እንደሚሳተፉ የሚጠበቅ መሆኑን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ አስተዋወቁ

ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ አስተዋወቁ
ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን ከፓን አፍሪካ የወጣቶች አመራር ጉባኤ ጎን ለጎን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ አስተዋውቀዋል።
ጉባኤው “የወጣቶችን አቅም – ለበለፀገች አፍሪካ” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል።
ጉባኤውን አስመልክቶ የተዘጋጀ ኤግዚቢሽንም ተከፍቷል።
በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የፌዴራል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ሚኒስትሮች፣ የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በጉባኤው የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ ማስተዋወቃቸውን ከሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top