Mols.gov.et

News

News

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን …

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ ነው – ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ 11ኛውን የሕብረት የስምምነት ተፈራርመዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
‎‎
የአሠሪና ሠራተኛ መልካም ግንኙነት መኖሩ ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዋነኛው መሣሪያ መሆኑንም አፅንዖት አንስተዋል።
‎በዕለቱ የተፈረመው የሕብረት ስምምነትም በአየር መንገዱ አመራርና በሠራተኛው መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥና ለተቋሙ ዘላቂ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አመላክተዋል፡፡

ይህ ዓይነቱ ስምምነት በሚኒስቴሩ የታለመውን ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት የመገንባት ራዕይ በተግባር የሚያሳይ ሲሉም ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የሕብረት ስምምነቱ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ቀጣይነት ያለው ስኬት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልፀዋል።
የሕብረት ስምምነቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዕድገት በማፋጠን የሠራተኞችን ጥቅም በዘላቂነት የሚያስከብር መሆኑንም አብራርተዋል።

Read More »
News

ስምምነቱ በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት…

ስምምነቱ በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ኢንስቲትዩቱ አስታወቀ
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር፤ ስምምነቱ ኢንስቲትዩቱ ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጋር የተያያዙ ስልጠናዎችን በማሻሻል በኩል ትርጉም ያለው ስራ እንዲሰራ ዕድል የሚፈጥርና በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ገልፀዋል።
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን የሚፈቱ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎች በኢንስቲትዩቱ እንደሚሰሩም አመላክተዋል።
ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ችግር ፈቺ የሆኑ ተኪ ቴክኖሎጂዎችን የመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራት በትኩረት እንደሚከናወንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በበኩላቸው፤ የቡና ጥራትን በመጠበቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የክህሎት ስልጠናዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ ካለው የማሰልጠን፣ የፈጠራ እና የምርምር ሥራዎች አቅም አንጻር አብሮ መስራቱ ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ የያዛቸውን ዕቅዶች ለማሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆንም ነው ያመላከቱት። መረጃው የኢኒስቲትዪቱ ነው።

Read More »
News

የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ተጠቀሚ መሆን ጀመሩ!

የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ተጠቀሚ መሆን ጀመሩ!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከ200ሺ በላይ ወጣቶች እና የመንግስት ስራተኞች ተመዝግበው ከ157ሺ በላይ ዜጎች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መውሰዳቸውን ተገለፀ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተጀመረው የ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች የዲጂታል ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩንም አብራርተዋል።
ሰልጣኞች የብቃት ማረጋገጫ ከማግኘት ባለፈ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማካኝነት የሥራ እድል ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውንም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂን ለማሳካት ሀገራችን የምታደርገው ጉዞ አካል ሲሆን በሦስት ኣመታት ውስጥ ሀገራችንን በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ ማድረግ የሚችሉ 5ሚሊዮን ሰዎችን ማብቃትን ዓላማው አድርጎ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

Read More »
News

የሰው ልጅን የፈጠራ ችሎታ ከቴክኖሎጂ ጋር ማጣመር

የሰው ልጅን የፈጠራ ችሎታ ከቴክኖሎጂ ጋር ማጣመር
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሳምንታዊ የጥናትና ምርምር ሴሚናር ከጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ጋር በተያያዘ በአራተኛው (4.0) እና በአምስተኛው(5.0) የኢንዱስትሪ አብዮቶች፣ በኢንዱስትሪ ሽግግርና በምዘና ሥርዓት ውጤታማነት ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ሪፖርት እና ዕቅድ ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመድረኩ ላይ የቀረበው የመጀመሪያው የጥናት ሪፖርት እንደሚያመለክተው ዓለም አቀፉ የኢንዱስትሪ አብዮት ከዲጂታላይዜሽን እና ከአውቶሜሽን ባለፈ የሰውን ልጅ የፈጠራ ችሎታ ከማሽኖች ጥምረት ጋር ወደሚያገናኘው አዲሱ ኢንዱስትሪ አብዮት 5.0 እየተሸጋገረ ይገኛል። ይህ ለውጥ በተለይም በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ዘርፍ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች አዳዲስና ዘመናዊ የክህሎት ዓይነቶችን እንዲላበሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
አራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ማሽኖች ያለ ሰው ንክኪ እንዲግባቡና ራሳቸውን ችለው ውሳኔ እንዲሰጡ የሚያደርግ ሲሆን አምስተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ደ ደግሞ ቴክኖሎጂ የሰውን ልጅ የመፍጠር አቅም እንዲያግዝ እንጂ እንዲተካው የማይፈለግበት ሥርዓት ነው።
ይህ አዲሱ አብዮት ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም እና ኢንዱስትሪዎች በችግር ጊዜ በቀላሉ የማይወድቁበትን ጥንካሬ መገንባት ላይ ትኩረት ያደርጋል።
ሆኖም አሁን ያለው የሀገሪቱ የቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ-ትምህርት አሁንም በአራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ቴክኖሎጂዎች ላይ ገና እየተንደረደረ መሆኑና በዲጂታል ፋሽን ንድፍ፣ በስማርት ማምረቻ እና በዘላቂነት ረገድ ሰፊ የክህሎት ክፍተት መኖሩ በሪፖርቱ ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ሰልጣኞች ማሽኖችን ከማንቀሳቀስ ባለፈ የፈጠራ አስተሳሰብ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ጠንቅቀው ማወቅ እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቷል።
ለዚህም እንደ መፍትሄ የቀረቡት ምክረ-ሀሳቦች የትምህርት ሥርዓቱን ማሻሻል፣ ቴክኖሎጂ በየጊዜው የሚቀየር በመሆኑ የዕድሜ ልክ ትምህርት ግንዛቤን ማስረጽ፣ የመንግስትና የኢንዱስትሪ ትብብርን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማሽኖች ሊተኳቸው የማይችሏቸውን የሰው ልጅ ልዩ ባህሪያት (Soft Skills) ማዳበር የሚሉ ናቸው። ይህም ሰልጣኞችን ከቀጣሪነት ባለፈ የቴክኖሎጂ መሪ እና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ተብሎ ይታመናል።
በተጨማሪም በሴሚናሩ ማጠናቀቂያ ላይ በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የምዘና ልምዶች እና ምሩቃን ብቃት ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ የሚያሳይ የጥናት ዕቅድ (Proposal) ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ይህ የጥናት ዕቅድ ወደፊት በዘርፉ ላይ የሚታዩ የአፈጻጸም እና የጥራት ችግሮችን ለመፍታት እንደ ዋነኛ ግብዓት ያገለግላል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል፡፡

Read More »
News

የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ቅንጅት..

የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ቅንጅት፤ ለተወዳዳሪ የሰው ኃይል ልማት!
ትውልድን ለመጪው ዘመን ማዘጋጀትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቱን ማረጋገጥ የጊዜው አጣዳፊ ጥያቄ ነው።
ይህ በተሟላ ደረጃ እውን እንዲሆን በትምህርትና ሥልጠና ተቋማት መካከል ያለው ቅንጅት መጠናከር የሰው ኃይል ልማታችን ከሥራ ገበያው ፍላጎት ጋር እንድናጣጣምና በሥራ ዕድል ፈጠራና በፈጠራ ሥነ-ምህዳሩ ላይ የሚኖረው አበርክቶ እንዲጎለብት ያደርጋል።
ላለፈው አንድ ዓመት በሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን የተቋም በህል ግንባታ ሥራችን አካል የሆነው ወርሃዊ “የማለዳ ውይይት” መርሃ-ግብር በዛሬው እለት በከፍተኛ ትምህርት፣ በቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ተቋማት መካከል ስትራቴጂካዊና እሴት-አካይ ቅንጅት መፍጠር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር ተካሂዷል።
ይህ መድረክ ተቋማቱ ለየብቻ ከመጓዝ ወጥተው ለጋራ ሀገራዊ ግብ እንዲሰናሰሉ የሚያስችል አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፍቷል።
በዚህም ከእውቀትና ክህሎት ባለፈ፣ ችግርን ወደ ዕድል የሚቀይሩና ሥነ-ልቦናዊ ጥንካሬ ያላቸው፤ በጠንካራ ሥነ-ምግባር የታነጹ፣ አቋራጭ መንገድን የማይሹና ለሀገራዊ ውጤት የሚተጉ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያፋጥኑና በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት የሰው ኃይል ልማታችን ዋነኛ ማጠንጠኛ መሆን ይኖርበታል፡፡
ከምክክሩ ጎን ለጎን የመድረኩ ተሣታፊዎች የኢትዮጵያን የሥራ ገበያ ሥርዓት እና የመንግስት አገልግሎት የፈጠራና የማሻሻያ ማዕከን በመጎብኘት በቀጣይ ተቀናጅቶ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተቀራርቦ ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል።

Read More »
News

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው የዘርፉ እሳቤ……
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከዚህ ቀደም የሚታወቁት በአጫጭር እና መደበኛ ፕሮግራም ያሰለጠኗቸውን ወጣቶች ሰርተፍኬት ሰጥተው በመሸኘት ነበር ፡፡ አሁን ግን ይህንን የተለመደ አሰራር የሚቀይር አዲስ እሳቤ ተቀርጾ በዘርፉ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል፡፡
እሳቤው ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸው ከሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ጋር የሚስማማ ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ የሚያስችል አዲስ እይታ ነው፡፡
በአሁን ወቀት ይህንን እሳቤ እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል፡፡ በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ 20% ቁጠባ እንዲቆጥቡ በማድረግ፣ ለሚመሰርቱት ኢንተርፕራይዝ መነሻ የሚሆን አቅም እንዲፈጥሩ እየተደረገ ይገኛል።
ከቴክኒካዊ ስልጠናው ጎን ለጎን በቀጣይ የኢንተርፕራይዝ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ስኬታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የኢንተርፕሪነርሺፕ እሳቤን ለመላበስ የሚያስችላቸውን ስልጠናም ከተቋማቱ ያገኛሉ፡፡
ኮሌጆች ያሏቸውን ማሽኖች ተጠቅመው እያመረቱ እንዲሰለጥኑ፣ እየሰለጠኑ እንዲያመርቱ የተቀመጠው አቅጣጫ ደግሞ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን ብቃትና ተወዳዳሪነት የሚያልቅ ሌላኛው የአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ገፅታ ነው፡፡
የቴክነኒክና ሙያ ተቋማት ጥራት ያለው ስልጠና አግኝተው፣ የኢንተርፕሪነርሺፕን ባህሪ ተላብሰው፣ በኮሌጆቹ ውስጥ በሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች እጃቸውን፣ ልባቸውንና አእምሯቸውን ቃኝተውና ኢንተርፕራይዝ መስርተው የሚወጡ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች የሚወጡባቸው ተቋማት ናቸው፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ዜጎች በስፋት የሚፈሩባቸው ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል፣ የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ ስብራት የሚጠግኑ ባለወርቅ እጆች የሚፈጠሩባቸውና ሀገርን የሚያልቁ ኩባንያዎች የሚፈለፈሉባቸው የፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነታቸውን ዕውን ማድረግ ደግሞ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተቀረፀው አዲሱ የክህሎት ልማት እሳቤ አዲሱ መዳረሻ ግብ ነው!

Read More »
News

ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ2,300 በላይ ባለሙያዎችን ለሥራ ገበያው በማቅረብ

ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ2,300 በላይ ባለሙያዎችን ለሥራ ገበያው በማቅረብ የዘርፉን ተወዳዳሪነት እያረጋገጠ ነው
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚያችን እምቅ አቅም ያለው ቢሆን፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት እና የሀገር በቀል ምግቦቻችን በዘመናዊው መስተንግዶ ውስጥ በሚፈለገው መጠን አለመካተታቸው በዘርፉ ገቢና ተወዳዳሪነት ላይ የራሱ የሆነ ጫና ሲፈጥር ቆይቷል።
ይህንን ክፍተት ለመሙላት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም የሆነው የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት፣ ተቋማዊ አሰራሩን በ ISO-21001:2018 ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ በማደራጀት ሰፊ የክህሎት ማበልጸጊያ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስድስት ወራት በዳቦና ኬክ ዝግጅት፣ በኩሊነሪ አርት፣ በምግብና መጠጥ ቁጥጥርና መስተንግዶ ዘርፎች ጥራት ያለው ተከታታይ ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል።
ከዚህም በተጨማሪ የሀገር በቀል ምግቦችን በሳይንሳዊ መንገድ በማጥናት ወደ ሆቴሎች የንግድ ስርአት (Menu) የማስገባት ስትራቴጂካዊ ሥራን በልዩ ትኩረት እሠራ ይገኛል።
በዚህም ባለፉት 6 ወራት ብቻ 2,346 አዳዲስና ነባር ባለሙያዎችን በክህሎት ማብቃት የቻለ ሲሆን፣ ይህም የዕቅዱን 67 በመቶ መሆኑ ተመላክቷል።
ይህ ስልጠና ባለሙያዎቹ በተሻለ ደመወዝ እንዲቀጠሩና የሆቴሎች አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል መንገድ ከፍቷል።
በተመሳሳይ፣ ኩሪፍቱ ሪዞርትና ሞናርክ ሆቴልን ጨምሮ ስድስት የሚሆኑ ሆቴሎች የኢንስቲትዩቱን የጥናት ውጤት መሠረት በማድረግ ባህላዊ ምግቦችን በሜኗቸው አካተው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ ይህም ባህላዊ ምግብና መጠጦቻችንን ለዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማስተዋወቅና የገበያ ዕድልን ለማስፋት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል፡፡

Read More »
News

ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ወደ ሥራ

ከስደት ተመላሽ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ወደ ሥራ የማስገባት ተግባር በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ
‹‹አካታችነት›› በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ የዋለው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ አንዱ የትኩረት አቅጣጫ ነው፡፡
በዚሁ መሰረት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ ስልጠናዎች ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ወጣቶችን ስደተኞችንና ሌሎችም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን በእኩል ተደራሽ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ይጠበቃል፡፡
የትኩረት አቅጣጫውን ወደ ተግባር ለመለወጥ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ከስደት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በሥደተኞች ላይ በሚሠሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተጎብኝተዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ ወጣቶችንና ተመላሾችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማሰልጠን ወደ ሥራ እንዲገቡ እያደረገ ይገኛል።
ስልጠናው ወጣቶች በቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ እንዲሰማሩና የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱ የሚያስችል ሲሆን ይህም ከጥገኝነት መንፈስ ተላቀው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እድል የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ ስደትን በዘላቂነት ለመከላከል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተገልጿል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወነ ያለው ተግባር መልካም መሆኑን ገልጸው በተለይም ወጣቶች የሚያገኙትን እውቀት ወደ ገቢ ምንጭ በመቀየር የተሻለ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። መረጃው የድሬዳዋ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው፡፡

Read More »
News

ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት (FTVTI) ከሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ ባህልና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር ይፋዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
ስምምነቱ በመደበኛና አጫጭር ስልጠናዎችን ለሶማሊያውያን ወጣቶች ደረጃውን የጠበቀና ጊዜውን የዋጀ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገብረእግዚአብሔር እና የሶማሊያ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ሀሰን ናቸው።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ በቀጣናው ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ደረጃ ለማሻሻል ለሰልጣኞችና ለአሰልጣኞች ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ እንደ ትልቅ ምዕራፍ በሚቆጠረው በዚህ ስምምነት መሰረት፤ ኢንስቲትዩቱ ለ25 ሶማሊያውያን ተማሪዎች የቅድመ-ምረቃ (Bachelor’s degree) የነፃ ትምህርት ዕድል ሰጥቷል።
ይህም ኢንስቲትዩቱ ለጎረቤት ሀገራት የላቀ የስልጠና እድሎችን ተደራሽ ለማድረግ የያዘው ተልዕኮ አካል መሆኑ ተገልጿል።
ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም አክለውም፤ ይህ ስምምነት የኢንስቲትዩቱ የቀጣናዊ ትስስር ስትራቴጂ ዋና አካል መሆኑንና የአቅም ግንባታ መርሃ ግብሩም ወደፊት በስፋት እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

Read More »
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ሪፎርም ትግበራ ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆኑ ተገለጸ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት አስተዳደር አገልግሎት ሪፎርም ትግበራ ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆኑ ተገለጸ
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሱፐርቪዥን ቡድን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በመገኘት፣ ተቋሙ የጀመረውን የተቀናጀ የሪፎርም እሳቤ እና ወደ ተግባር ምዕራፍ የተሸጋገሩ ሥራዎችን የመስክ ምልከታና የድጋፍ ሥራ አከናውኗል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባደረገው ቆይታ፣ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥና የአስተዳደር ማሻሻያ ተግባራትን ወደ ወሳኙ “የተግባር ምዕራፍ” ማሸጋገሩን አረጋግጧል።
ይህም ሚኒስቴሩ እንደ ሀገር የተቀመጠውን የሪፎርም ግብ ለማሳካት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና ለሌሎች የመንግስት ተቋማትም አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።
ዲጂታላይዜሽን እና የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO) በምልከታው ወቅት ሚኒስቴሩ ውጤታማ በሆነ መንገድ እየተገበራቸው የሚገኙ ቁልፍ ሥራዎች በበጎ ተነስተዋል፡፡
ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ዜጎች ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና እንግልት የሌለበት አገልግሎት የሚያገኙባቸው አሰራሮች መዘርጋቱም ተገልጿል፡፡
የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም ተቋማዊ ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ የማድረግ ሂደት ትልቅ እመርታ አሳይቷል።
ሚኒስቴሩ የሪፎርም እሳቤዎችን እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በዋናው መስሪያ ቤት ብቻ ሳይወሰን፣ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በማውረድ ክልሎችን ለማብቃት እያደረገ ያለው ድጋፍ የሪፎርሙን ውጤታማነት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተጠቁሟል። በክልሎች ደረጃ የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎች መጀመራቸውም እንደ አንድ ትልቅ ጥንካሬ ተነስቷል።
በትግበራ ምዕራፍ የታቀዱ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ወደ ቀጣዩ “የማፅናት ምዕራፍ” ለመሸጋገር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚገባ በኮሚሽኑ ድጋፍና ክትትል ቡድን ተጠቁሟል፡፡

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top