Mols.gov.et

News

News

የዓለም ባንክ ለወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡

የዓለም ባንክ ለወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ከዓአለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ የማህበራዊ ጥበቃና ሥራ አተገባበር ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሮበርት ቼዝ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት፤ መንግስት ለወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለማላቅ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የማዘመን ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዓለም ባንክ ድጋፍ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በመጀመሪያ ዙር የሥራ ላይ ልምምድ ካደረጉ ወጣቶች መካከል 93 በመቶ ከሥራ ጋር ማስተሳሰር መቻሉንም አመላክተዋል፡፡
18 የሚሆኑ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን በረጃ የማሻሻል እና በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ያመላከቱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ባንኩ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠየቀዋል፡፡
የዓአለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ የማህበራዊ ጥበቃና ሥራ አተገባበር ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሮበርት ቼዝ በበኩላቸው፤ በመጀመሪያው ዙር በወጣች የሥራ ላይ ልምምድ የተገኘው ውጤት የሚያበረታታ ነው ብለዋል፡፡
ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታሳቢ በማድረግ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ የሚሆን እንደሆነም አመላክተዋል፡፡
በጨረታ ሂደት የሚስተዋሉ መዘግየቶችን በመቅረፍ ባንኩ ለወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያደርገውን ድጋፍም አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡
ከውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አኳያ የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማሰማራት የተጀመሩ ሥራዎችን ያደነቁት ዶ/ር ሮበርት ቼዝ ለዓለም የሥራ ገበያ የሚቀርበው የሰው ሃይል የመዳረሻ ሀገራትን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና እንዲሰጥና እንደ ጀርመን ያሉ ሀገራትን ታሳቢ አድርጎ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

ሁሉም ሲያሸንፍ ሀገር ትቀናለች!

ሁሉም ሲያሸንፍ ሀገር ትቀናለች!
ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ላለፉት ሶስት ሳምንታት ሲካሄድ የሰነበተው የስታርትአፕ ኢትዮጵያ የሥራ ፈጣሪዎችና የአዳዲስ ግኝቶች ባለቤቶች የውድድር መድረክ ተጠናቀቀ፡፡
በዚህ የስታርትአፕ ኢትዮጵያ የሥራ ፈጣሪዎችና የአዳዲስ ግኝቶች ባለቤቶች የውድድር መድረክ እና አውደ ርዕይ ማጠናቀቂያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት
ሁሉም ተሳታፊዎች አሸናፊ በሆኑበት ላለፉት ሶስት ሳምንታት ሲካሄድ የሰነበተው የስታርትአፕ ኢትዮጵያ የሥራ ፈጣሪዎችና

የአዳዲስ ግኝቶች ባለቤቶች የውድድር መድረክ እና አውደ ርዕይ ማጠናቀቂያ ፕሮግራም ላይ ተገኝቼ የሀገር ተስፋ የሆኑትን ብርቅዬ ወጣቶች የማበረታታት እድል በማግኘቴ እጅግ ደስ ብሎኛል! ተሸላሚዎች እንኳን ደስ ያላችሁ! ብለዋል፡፡

አክለውም ስታርትአፖች በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በኢኮኖሚ ልማት ውስጥ በሚጫወቱት ወሳኝ ሚና ለፈጣን የኢኮኖሚ እድገትና ብልፅግና አንቀሳቃሽ ሞተር ናቸው:: አዳዲስ ሀሳቦችን እና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ምርታማነትንና የስራ ዕድል ፈጠራን ያስፋፋሉ:: ከአዳዲስ የገበያ ፍላጎቶች ጋር ለመላመድ ያላቸው ቅልጥፍና እና ብቃታቸው ኢንዱስትሪዎችን እንዲጎለብቱ እና አዳዲስ ምርቶችን እንዲፈጥሩም ያስችላሉ::
ይህ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን አመራርና አነሳሽነት እንዲሁም በሰባት ተቋማት ትብብር (የጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት፣ የሳይንስና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ልማት ኢንስቲቲዩት እና የገበያ ባለስልጣን) በሳይንስ ሙዚየም ሲካሄድ የቆየው አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብና እና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዘው የቀረቡ ወጣቶች ልምዳቸውን የተለዋወጡበት ስታርትአፖች የመተዋወቅ እድል ያገኙበት ውጤታማ ስራ ፈጣሪነት የተበረታታበትና የፈጠራ ስራዎች እንዲጎለብቱ ምቹ ምህዳር የተፈጠረበት መርሃ ግብር ነበር:: ሥለሆነም ስታርትአፖች ይህንን የተፈጠረ ምቹ መደላድል ተጠቅማችሁ የላቀ ውጤት እንደምታስመዘግቡ ሙሉ እምነቴ ነው ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

የጤናውን ዘርፍ አቅም ማሳደግ ነገ ማየት የምንፈልጋትን የበለፀገች ኢትዮጵያ ጤናማ መንገድ የመቅረፅ አካል ነው::

የጤናውን ዘርፍ አቅም ማሳደግ ነገ ማየት የምንፈልጋትን የበለፀገች ኢትዮጵያ ጤናማ መንገድ የመቅረፅ አካል ነው::
በጤናው ዘርፍ ሥራ ስራ ስምሪትንና የክህሎት አቅም ግንባታን ለማሳደግ በትብብር ለመስራት ስልቶችን ለመንደፍ ከጤና ሚንስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር ውጤታማ ምክክር ሰለማድረጋቸው ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል፡፡
በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሚገኙ የጤና ዘርፍ የሥራ እድል ፍላጎት በተገቢው ክህሎትና አስተሳሰብ በተገነባ ብቁ የጤና ባለሙያዎች አቅርቦት ለማሟላት አቅማችንን በትብብር የማሳደግ ስልቶች ላይ በትኩረት መወያየታቸውንም ገልጸዋል፡፡
በጤናው ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ለሥራ ገበያው በማቅረብ ዜጎችንና ሀገርን ለመጠቀም እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ የትብብሩ ቁልፍ ተግባር ይሆናል::
ሙያዊ ክህሎትን ከማሳደግ ባሻገር የውጭ ሀገር ሥራ ዕድሎችን በተገቢው በማሰስ የሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎቻችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለጤና አጠባበቅ ምህዳሩ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ የሚያግዙ መንገዶችን መፍጠር በትኩረት የምንሰራበት ይሆናል።
አክለውም ወ/ሮ ሙፈሪሃት ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና አጠባበቅ ዘርፉን ለማጠናከር እና ለጤና ሰራዊታችን በሀገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድልን ለማስፋት በትብብር ለመስራት ያሳዩትን ቁርጠኝነት እጅጉን አደንቃለሁ! ለነበረን ጥልቅ እሩቅ አላሚና ችግር ፈች መንገዶችን ጠቋሚ ውይይት ክልብ አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አመራሮች በፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ከተቋቋመውና …

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አመራሮች በፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ከተቋቋመውና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱንና እና የተጠሪ ተቋማትን የበጀት ዓመቱን ዕቅድ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ከሚገመግመው የሱፐርቪዥን ቡድን ጋር የመግቢያ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የሚመራው ይህ የሱፐርቪዥን ቡድን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በተከናወኑ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮች፣ በሥራ ገበያ አስተዳደር ስርዓትና በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገልግሎት ላይ በማተኮር ምልከታውን ያካሄዳል፡፡
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን አፈጻጸም መነሻ በማድረግ ከፖሊሲ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች ላይ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን መለየት የሱፐርቪዥን ምልከታው ከሚያተኩርባቸው ጉዳዮች መካከል ዋንኛው መሆኑ ተገልጿል፡፡
ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታትና ማነቆዎችን ለመፍታት መወሰድ ያለባቸውን እርምጃዎች ማመላከትም ከቡድኑ የሚጠበቅ ሌላው ውጤት መሆኑም በመድረኩ ተብራርቷል፡፡

Read More Âť
News

ከውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ኤጀንሲዎች ማህበራት የቦርድ አባላት ጋር…

ከውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ኤጀንሲዎች ማህበራት የቦርድ አባላት ጋር ዜጎችን በውጭ ሀገር የሥራ ገበያ ላይ ደህንነታቸውና ክብራቸው ተጠብቆ በውጤታማነት ለማሰማራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጏል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሥርዓትንና ህግን እንዲሁም የዜጎችን ክብር በጠበቀ መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን የሚያስችል የሪፎርም ሥራዎችን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩ ዜጎችንም ሆነ ሀገርን ከዘርፉ ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው በውይይቱ በጉልህ ተነስቷል፡፡
ዜጎችን ለእንግልትና ለአደጋ የሚዳርጉ ህገወጥ ድርጊቶችን ከመግታት አንፃር መንግስትና በውጭ አገር ሥራ ሥምሪት ላይ የተሰማሩ ኤጀንሲዎች በጥምረት መስራት እንደሚኖርባቸውም አፅንዖት ተሰጥቶት ተነስቷል፡፡
ከተለያዩ መዳረሻ ሀገራት የሚቀርበውን የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ለማሟላት በሚያስችል መልኩ ኤጀንሲዎች ራሳቸውን ማጠናከርና አቅማቸውን ማሳደግ እንደሚኖርባቸውም ከመግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

Read More Âť
News

የቤተሰብ ንግድ ቀጣይነት ላለው ሥራ ዕድል ፈጠራ !

የቤተሰብ ንግድ ቀጣይነት ላለው ሥራ ዕድል ፈጠራ!
በዓለም ላይ”የቤተሰብ ንግድ“ዘላቂ የሥራ ዕድል በመፍጠር እና ፈጠራን በማበረታታት የሀገራት የኢኮኖሚ ሞተር በመሆን የማይተካ ሚና ይጫወታል፡፡
አሁን ላይ ባደጉት ሀገራት የ”ቤተሰብ ንግድ“ በትሪሊዮን የሚቆጠር ዶላር ገቢ በማመንጨትና ለበርካቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ውስጥ ጫወታ ቀያሪ ከሆኑ ተዋንያን መካከል ተጠቃሹ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
እ.አ.አ በ1938 በአነስተኛ የንግድ ድርጅትነት ተመስርቶ ወደ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያነት ያደገውና“በሊ ቤተሰብ” የሚመራው የደቡብ ኮሪያው ሳምሰንግ ኩባንያ ለቤተሰብ ንግድ ውጤታማነት እንደማሳያነት ይቀርባል፡፡
በሀገራችን በቤተሰብ ንግድ ደረጃ ጎልተው የወጡ የንግድ ድርጅቶች ያሉ ቢሆንም በአጠቃላይ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስትራቴጂያችን መሰረት የሚፈጠሩት ኢንተርፕራይዞች ዘላቂና ውጤታማ እንዳይሆኑ እንደምክንያት ከሚያነሱት ተግዳሮቶች መካከል የማምረቻና የመሸጫ ቦታ ችግሮች በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡
ይህ እና መሰል ችግሮች ሳያንበረክካቸው ውጤታማ የሆኑ በርካታ ኢንተርፕራይዞችና የንግድ ድርጅቶች በሀገራችን ይገኛሉ፡፡ ከዚህ አንፃር’አባይነሽ ፋርም’ በግንባር ቀደምነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው፡፡
‘አባይነሽ ፋርም’ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ የሚገኝ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ማዕከል ነው፡፡
ማዕከሉ በአምስት የቤተሰብ አባላት በቤተሰቡ ቦታ ላይ ሲመሰረት አራት የወተት ላሞችን ብቻ በመያዝ ነበር ሥራ የጀመረው፡፡
የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ ገዛኸኝ እንደሚገልጹት በ2006 ዓ.ም በአራት የወተት ላሞች የጀመረው ሥራ አሁን ላይ ከ60 በላይ የውጭ ዝርያ ያላቸው ከብቶች ባለቤት ሆኗል፡፡ በዚህም በቦንጋና አከባቢው በቀን በአማካይ 500 ሊትር የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡
ከወተት ምርት አቅርቦት ባሻገር ድርጅቱ የእሴት ሰንሰለትን መሰረት ባደረገ ሥራው የእንስሳት መኖ ዝግጅት፣ አቅርቦት እና የእንስሳት ዘር ማሻሻል ላይ በማተኮር ከራሱ አልፎ ለአካባቢው ህብረተሰብ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡
ሳይንሳዊ በሆነው በዚህ የእንስሳት መኖ ዝግጅት፣ አቅርቦት እና የእንስሳት ዘር ማሻሻል ሥራ
ድርጅቱ ከአንድ ላም እስከ 45 ሊትር ወተት ማግኘት እንደተቻለ ነው የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ የሚናገሩት፡፡
በርካታ ፈተናዎችን አልፎ አሁን ላይ የደረሰው አባይነሽ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ማዕከል በመስኩ በቂ የትምህርት ዝግጅትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን ጨምሮ ከ62 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የቻለና በክልሉ በአርአያነት የሚጠቀስ ድርጅት ለመሆን ችሏል፡፡
በቀጣይም ሥራውን በማስፋት ከቦንጋ ባለፈ በአጎራባች ወረዳና ዞኖች ጭምር በወተት ምርት፣ በእንስሳት መኖ እና በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያ አቅርቦት የአከባቢው ህብረተሰብ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ በሂደቱ ለበርካቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ያደረገውን ተቋማዊ ሪፎርም ተከትሎ ቀደም ብሎ በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በመለየት “ለቤተሰብ ንግድ” ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡

Read More Âť
News

የዘርፉን አዲስ እሳቤ …

“የዘርፉን አዲስ እሳቤ በተገቢው መልኩ ለመተግበር የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል።”
ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሃመድ የሥራና ክህሎት አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት ከአዲስ አበባ መስተዳድር የሥራና ክህሎት፣ የሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ዲኖች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሥራና ክህሎት አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሃመድ የሚኒስቴር መ/ቤቱ የሰፐር ቪዥን ቡድን አባላት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዘርፉ ሥራዎችን ላይ ቅኝት ሲያካሄድ መቆየታቸውን ገልፃዋል፡፡
ባለፉት 20 ቀናት በተካሄደው የመስክ ምልከታ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናን ከአዲሱ የዘርፉ እሳቤ መሠረት ከመቃኘት አንፃር ተስፋ ሰጪ ጅምሮች መስተዋላቸውን የገለፁት ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ በዘርፎች መካከል ቅንጅትን ከመፍጠርና የውጭ አገር የሥራ ሥምሪት ላይ ተሳታፊ ለሚሆኑ ዜጎች ተገቢውን ሥልጠና እና ምዘና ከመስጠት አንፃር ግን ክፍተት መስተዋሉን አስታውቀዋል፡፡
ክፍተቶቹን መነሻ በማድረገም በመድረኩ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍን አዲስ እሳቤ፣ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓትን እና የውጭ አገር ሥራ ስምሪትን የተመለከቱ ገለፃዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እየተገበረ የሚገኘውን የዘርፉን አዲስ እሳቤ መነሻ በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትንና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሀመድ በመጠቆም ለሥራ ወደ ውጭ አገራት የሚሰማሩ ወገኖች ተገቢውን ሥልጠና አግኝተው፣ ተመዝነው እንዲሁም ህጋዊ መንገድን ተከትለው እንዲሄዱ ለማስቻል የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

Read More Âť
News

የሊቢያ የሥራና መልሶ ማቋቋም ሚኒስትር …

የሊቢያ የሥራና መልሶ ማቋቋም ሚኒስትር ክቡር ሚስተር አሊ አቡአዙም ጋር በጋራ መስራት በምንችልባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አካሂደናል፡፡

ረጅም ዓመታትን ባስቆጠረው የኢትዮጵያና የሊቢያ ግንኙነት በአጠቃላይ ትብብር መስክ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ የተለያዩ የስምምነት ሰነዶች መፈረማቸውን መነሻ በማድረግ በሥራ ሥምሪት መስክ በጋራ ለመስራት በሚያስችሉን ነባራዊ ሁኔታዎች ላይም ተወያይተናል፡፡

በዚሁ መነሻነት ኢትዮጵያ በከፊል የሰለጠነ እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለሊቢያ የሥራ ገበያ ለማቅረብ በሚያስችላት ሁኔታዎች ላይ መክረናል፡፡

በሊቢያ ሥራ ገበያ ላይ ካለው የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን እንዲሁም ሊቢያን መልሶ በመገንባት ሂደት በሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሀይል ስምሪት ላይ የበኩላችንን ሚና ለመወጣት ውይይት አካሂደን ከስምምነት ላይ ደርሰናል፡፡

በተለያየ መንገድ ዜጎች ለህገወጥ አዘዋዋሪዎች ተጋላጭ መሆናቸ ይታወቃል:: ይህ የጀመርነው ስምምነት ይህንን ተጋላጭነት የሚቀንስ በሂደትም የሚያስቀር ይሆናል ተብሎ ይታመናል::

Read More Âť
News

ሚኒስቴሩ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ዕቅድ አፈፃፀሙ እና…

ሚኒስቴሩ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ዕቅድ አፈፃፀሙ እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያየ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ላይ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ዕቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ሲያደርጉ ቆይቷል፡፡
የዜጎች መብት፣ ደህነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ባለመው የጋራ ዕቅድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት እና የቀጣይ የጥኩረት አቅጣጫዎች ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡
በዕቅድ አፈፃፀም ግምገማው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖን ጨምሮ የሁለቱም ተቋማት ክፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በዚህም ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ ስርዓት በታገዘው የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት የመዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት፣ በስምሪቱ የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማካተት እንዲሁም ኤምባሲና ቆንስላዎቻችን የዜጎችን መብት፣ ደህነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የተጀመረው ሥራ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እንደተገኙበት ተጠቁሟል፡፡
በጋራ ዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ጠንካራ ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና ክፍተቶችን በማረም በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የዜጎችን መብት፣ ደህነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ሥራን ውጤታማነት ለማላቅ የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ መዘጋጀቱም በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል፡፡

Read More Âť
News

ሚኒስቴሩ የጋራ ዕቅድ አፈፃፀሙን ከልማት ባንክ ጋር ገመገመ

ሚኒስቴሩ የጋራ ዕቅድ አፈፃፀሙን ከልማት ባንክ ጋር ገመገመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡
ስምምነቱን መሰረት በማድረግም በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና በሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ፈጠራ ዙሪያ የጋራ ዕድቅድ ታቅዶ ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በተገኙበት የዕቅድ አፈፃፀሙ ተገምግሟል፡፡
በዚህም ተቋማዊ ቅንጅት ለዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ያለውን ፋይዳ በመረዳት እና የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችን ስኬት ለማላቅ ባለመው የጋራ ዕቅድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መገኘቱ የተገመገመ ሲሆን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችም ላይም ውይይት አድረዋል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top