Mols.gov.et

News

News

የኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ለሀገር ብልጽግና…

“የኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ለሀገር ብልጽግና”፦ ታላቁ አውደ ርዕይ በመስቀል አደባባይ በደመቀ ሁኔታ ተከፈተ!
የመዲናችን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆኑት ኢንተርፕራይዞች የሥራ ውጤታቸውን ይዘው አደባባይ ወጥተዋል! በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት የሚካሄደውና ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆየው ዓመታዊ የኢንተርፕራይዞች ሳምንት አውደ ርዕይና ባዛር በመስቀል አደባባይ በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በመክፈቻው ላይ እንደገለጹት፣ መንግስት የሰው ኃይልን ወደ ምርታማነት ለመቀየር ባደረገው ጥረት ባለፉት ዓመታት ብቻ ከ2 ሚሊዮን በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በበኩላቸው፣ ዘርፉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና ለኢንዱስትሪ ሽግግር ያለውን ፋይዳ አብራርተዋል። ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ብቻ ለ11,605 ኢንተርፕራይዞች ከ13.5 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩንም አስታውቀዋል፡፡
በተመሳሳይ ለ5,983 አንቀሳቃሾች 2.8 ቢሊዮን ብር ብድር የቀረበ ሲሆን፣ ለ1,571 ኢንተርፕራይዞች የ706.3 ሚሊዮን ብር የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ ተደርጓል። 10,921 ኢንተርፕራይዞች ደግሞ ከጥቃቅን ወደ አነስተኛ ደረጃ መሸጋገራቸው በመድረኩ ተገልጿል፡፡

Read More Âť
News

ከአሰልቺ አሠራር ወደ ቀልጣፋው የአገልግሎት ማዕከል(መሶብ)

ከአሰልቺ አሠራር ወደ ቀልጣፋው የአገልግሎት ማዕከል(መሶብ)
የሥራ ባህል ለውጥ በሀገራችን ኢትዮጵያ ፕሮጀክቶች ጀምሮ በመጨረስ እና የመንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት በማዘመን ሂደት እየተገለጠ ይገኛል፡፡
ከልማት ፕሮጀክቶች አኳያ በኮሪደር ልማትና በሌሎችም ግንባታዎች ላይ የምናየው የቀንና ሌሊት ትጋት፣ ሥራን የዜግነት ክብር አድርጎ የማየት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ያሳያል። በተመሳሳይ መንግስት ዜጎችን ከእንግልት ለማዳን በመሶብ አንድ ማዕከል ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለዜጎች በማቅረብ ረገድ አርአያ የሚሆን ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎታቸውን እያቀረቡ ከሚገኙ ተቋማት መካከል ደግሞ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠቃሽ ነው፡፡ ሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ዜጎች የሥራ ፈቃድ እድሳት እና ክሊራንስ የመሳሰሉ አገልግሎቶች እየሰጠ ይገኛል፡፡
በተመሳሳይ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተለያዩ የሥራና ክህሎት ቢሮ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ አስገብተው ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽ ከተደረገባቸው ክልሎች አንዱ የሆነው የሲዳማ ክልል በማዕከሉ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች የኢንተርፕራይዝ ምዝገባ እና የሥራ ምዝገባ ይገኙበታል፡፡ በዚህም ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ መሆኑ የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ ገልጸዋል፡፡
የሥራ ባህል ምንነት በዋናነት የሚለካው ለተገልጋይ በሚሰጥ ክብርና ለጊዜ በሚሰጥ ዋጋ ነው ያሚሉት አቶ ከፍ ያለው ቀደም ሲል አንድ ዜጋ የሥራ ምዝገባ፣ ንግድ ለመጀመር ወይም ልዩ ልዩ ፈቃዶችን ለማግኘት በየመሥሪያ ቤቱ ሲንከራተትና ሲንገላታ ይስተዋል ነበር። አሁን ግን የመሶብ አንድ ማዕከል ይህንን እንግልት በማስቀረት ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር እንዲያገኙ አስችሏል ብለዋል።
እንደ አቶ ከፍያለው ገለጻ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት በማድረግ አዲስ የሥራ ባህል መፍጠር አስችሏል።
አገልግሎቱ ተደራሽ በሆነባቸው አካባቢዎች እንደ ኮሪደር ልማቱ ሁሉ፣ በመሶብ ማዕከላትም የሚታየው ቁርጠኝነት አገልግሎቶች በተቀመጠላቸው የሰዓት ገደብ (Service Level Agreement) እንዲጠናቀቁ ከማድረጉም በላይ የመንግሥት ሠራተኛው ለዜጎች ያለውን አገልጋይነትና ለሥራው ያለውን ታማኝነት በተግባር የሚያሳይበት መድረክ ሆኗል።
አንድ ፕሮጀክት በወቅቱ ሲጠናቀቅ ሀገር እንደምታተርፈው ሁሉ፣ አንድ ዜጋ አገልግሎትን ያለ እንግልት ሲያገኝም ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል። እንግልት ሲቀንስ ዜጋው ጊዜውንና ጉልበቱን ምርታማነት ላይ ያውላል።
መሶብ አንድ ማዕከል ይህንን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር፣ ዜጎች በሀገራቸው የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና በኢኮኖሚው ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማድረጉን ቀጥሏል።

Read More Âť
News

“የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን በማጠናከር ረገድ …

“የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን በማጠናከር ረገድ ስኬታማ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው”፤
የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት
በሀገራችን የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን (Entrepreneurship Ecosystem) በማጠናከርና ወጣቶች ወደ ሥራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ አዳዲስ የንግድ ሐሳቦችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ስልታዊ ድጋፎችን እያከናወነ ይገኛል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሀሰን ሁሴን እንደገለጹት፤ ተቋማወጣቶች የራሳቸውን የፈጠራ ሐሳብ ይዘው ሲመጡ፣ ያ ሐሳብ ወደ ውጤታማ ኢንተርፕራይዝ እንዲያድግ የሚያስችል የክህሎት፣ የማማከርና የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት ላይ ነው።
ዶክተር ሀሰን አክለውም፣ ከክህሎት ድጋፍ በተጨማሪ የገበያና የፋይናንስ ትስስር ለሥራ ፈጣሪዎች ስኬታማነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ከባንኮችና ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ለፈጣሪዎች የብድርና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን የማመቻቸት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
አሁን ላይ በገበያ ውስጥ የሚታዩ ስኬታማ ስታርታፖች የኢንስቲትዩቱ ስልታዊ ድጋፍ ውጤቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ወጣቶች ያላቸውን የፈጠራ አቅም በመጠቀም ወደ ሥራ ፈጣሪነት እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ የኢንተርፕረነርሽፕ ንቅናቄ በሀገራችን ያለውን የሥራ አጥነት ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የኢኮኖሚ ዕድገቱን ለማፋጠን እንደ ትልቅ መፍትሔ የሚወሰድ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።

Read More Âť
News

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ እና የሀብት መፍጠሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል
በድሬዳዋ ከተማ ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን በአዲሱ የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ እንዲሁም የመሰረታዊ ክህሎት (Basic skill modules) ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ።
ይህ አዲስ ስትራቴጂ ‹‹ከስልጠና በላይ›› በሚል መሪ ቃል የተቀረጸ ሲሆን ዋና ዓላማውም የሰልጣኞችን የአስተሳሰብ አድማስ በማስፋት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ እና የሀብት መፍጠሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል ነው።
ስትራቴጂው በተለይም በፋብሪኬሽን ኢንጅነሪንግ እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ነጻነትን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የስልጠናው ይዘት በዋናነት አራት ስትራቴጂካዊ የትኩረት መስኮችን የተከተለ ሲሆን እነሱም የዘርፉን አስተዳደር ማጎልበት፣ የስልጠናውን አግባብነትና ጥራት ማረጋገጥ፣ ሰልጣኞችን ለሥራ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎቶችን ማስታጠቅ እንዲሁም ምርምርና ፈጠራን ማበረታታት ናቸው።
ስልጠናው ገበያ መር መሆኑ የሥራ ገበያው የማይፈልገውን ሙያ በማሰልጠን የሚባክነውን ሀብትና የሚፈጠረውን ሥራ አጥነት ለመቀነስ እንደሚያስገድድ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ውስጥ የተቀረጹ አምስት መሰረታዊ የክህሎት ሞጁሎች ለአሰልጣኞቹ ቀርበዋል።
አነዚህም ልል ክህሎቶች (Soft Skills) ፣ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎቶች፣ ስነ-ምግባርና ዜጋዊ ኃላፊነት፣ የሥራ ፈጣሪነት አስተሳሰብን ማሳደግ እንዲሁም የንግድ ሥራዎችን መንደፍና ማስጀመር የሚሉ ናቸው።
እነዚህ ሞጁሎች ሰልጣኞች ከመደበኛው የተግባር ስልጠና በተጨማሪ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሥራ ዓለም ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን ሁለንተናዊ ብቃት እንዲላበሱ ለማድረግ ታስበው የተዘጋጁ መሆኑ ተጠቅሷል።

Read More Âť
News

ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም ያለው የቱሪዝም ዘርፍ

ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም ያለው የቱሪዝም ዘርፍ
የቱሪዝም ዘርፍ ያለውን ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም መነሻ በማድረግ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ እየሠጠ እንደሚገኝ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ኢንስቲትዩቱ የሥራ አጥነትን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍና የኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስልታዊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
የኢንስቲትዩቱ የምርምርና ማማከር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም እንደገለጹት፤ የቱሪዝም ዘርፍ በባህሪው ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ፣ ኢንስቲትዩቱ የሚሰጣቸው ስልጠናዎች ከገበያው ተጨባጭ ፍላጎት ጋር እንዲጣጣሙ እየተደረገ ነው።
በተለይም ወጣቶች በዘርፉ ሰልጥነው ሲወጡ የራሳቸውን ቢዝነስ እንዲጀምሩ የሚያስችል የክህሎትና የሥራ ፈጠራ ስልጠናዎችን በማቀናጀት፣ ዜጎች መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎችም የሥራ ዕድል የሚፈጥሩበት ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ይታሰብ አክለውም፣ አሁን ላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱ አዳዲስ የቱሪዝም ቴክኖሎጂዎችን በስልጠና ክፍሎቹ በማስተዋወቅ ሰልጣኞች በዘመናዊ መንገድ አገልግሎት መስጠት የሚችሉበትን ብቃት እንዲላበሱ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

Read More Âť
News

“ከፈጠራ ሐሳብ ወደ ተጨባጭ ተግባር’’

“ከፈጠራ ሐሳብ ወደ ተጨባጭ ተግባር’’
የክህሎት ባንክ የሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን ችግር ፈቺ ተግባር በማሸጋገር ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለፀ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም በሆነው በኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሾር የሚገኘው “የክህሎት ባንክ” (Skill Bank)፣ የፈጠራ ስራዎችን በማልማትና ወደ ንግድ ማዕቀፍ (Commercialization) በማሸጋገር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
ማዕከሉ በተለይ በክረምት መርሃ-ግብር እና በ“ስኪል ኢትዮጵያ ስታርታፕ” ፕሮግራም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ለገበያ በማቅረብ ለሀገራዊ ምርታማነት የላቀ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ነው፡፡
የኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂና ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፀዳለ ተክሉ እንደገለጹት፤ ስኪል ባንክ ከመረጃ ቋትነት ባለፈ አዳዲስ የፈጠራ ሐሳቦች ተቀርጸው ወደ ተግባር የሚቀየሩበት ህያው የፈጠራ መድረክ (Innovation Hub) ነው ።
እስካሁንም ከ600 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ160 በላይ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲፈጠሩ ያደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በርካታ ተኪ ቴክኖሎጂዎች ወደ ተጠቃሚው ማህበረሰብ እየደረሱ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ወይዘሮ ፀዳለ ገለጻ፣ በማዕከሉ ከለሙና ወደ ንግድ ከተሸጋገሩ ስኬታማ ቴክኖሎጂዎች መካከል በኢንተርኔት የታገዘ ስማርት መስኖ (IoT Smart Irrigation) በአፋርና ሶማሌ ክልሎች በንግድ ደረጃ ሼል ላይ የዋለ ሲሆን፣ አፈር አልባ የሆነው የ”ሃይድሮፖኒክ” የእንስሳት መኖ ማምረቻ ቴክኖሎጂም ከኢንተርፕራይዞች ጋር በተፈጠረ ትስስር ምርቱን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።

Read More Âť
News

የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የሪፎርም ትግበራውን ወደ ተግባር አሸጋገረ

የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የሪፎርም ትግበራውን ወደ ተግባር አሸጋገረ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የቴክኖሎጂና የሥራ ባሕል ዕድገትን የሚመጥን ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችለው የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ወደ ተግባር ምዕራፍ መሸጋገሩ ተገለጠ።
ይህንንም ተከትሎ ቢሮው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ለአመራሮች፣ ለዓብይና ለቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ለሁለት ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና በመስጠት ላይ ነው።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር አማካሪ አቶ አዝመራ ከበደ የሪፎርም ሥራዎችን በአግባቡ መተግበር ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎትን በማቅረብ ረገድ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልፀዋል።
ሪፎርሙ በሰው ሀብት ልማት ላይ ትኩረት የሚያደርግ መሆኑን የጠቀሱት አማካሪው፣ የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ የበቃና ዝግጁ የሆነ የሰው ኃይል መፍጠር እንደሚገባም አስረድተዋል።

Read More Âť
News

ከ26 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረው የከተማ ግብርና…

ከ26 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረው የከተማ ግብርና
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 8 ወራት ብቻ በከተማ ግብርና ዘርፍ ከ 26 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሥራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን እንደገለጹት፤ 2,088 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም በቅጥር ከ 26 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡
በከተማዋ ባለፉት 8 ወራት ከተፈጠረው 287 ሺህ በላይ ቋሚ የሥራ ዕድል ውስጥ የከተማ ግብርና የ 9.3 በመቶ ድርሻን ይዟል።
በከተማዋ የሥራ ዕድል ሊፈጠርባቸው የሚችሉ 44,307 የከተማ ግብርና ጸጋዎች ተለይተው ወደ ሥራ መገባቱን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ ኢንተርፕራይዝ በማደራጀት ብቻ 17,404 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
የከተማ ግብርና ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር የተሻገረ ፋይዳ እንዳለው የጠቆሙ ዳይሬክተሩ ለነዋሪዎች የዕለት ተዕለት የምግብ ፍጆታ የሚውሉ (አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ዶሮና እንቁላል…) የመሳሰሉ ምግቦች በራስ ግቢና አካባቢ በማምረት የኑሮ ውድነትን መቋቋም ያስችላል ብለዋል።

Read More Âť
News

የዘርፍን ውጤታማነት የማላቅ ግብ ያለው ቴክኒካዊ ድጋፍና ክትትል

የዘርፍን ውጤታማነት የማላቅ ግብ ያለው ቴክኒካዊ ድጋፍና ክትትል
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በዘርፉ የታቀዱ የለውጥ አጀንዳዎችና ስትራቴጂካዊ ግቦች ውጤታማ መሆናቸውን ለማረጋገጥ፣ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የሚከናወን መጠነ-ሰፊ የቴክኒክ ድጋፍና የመስክ ክትትል ሥራ ጀምሯል።
የክትትልና ድጋፍ ሥራውን የሚመሩት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነቢሃ መሐመድ እንደገለጹት፤ ይህ የመስክ ምልከታ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሀገራዊ ተልዕኮውን በስኬታማነት ለማስፈፀም የቀረፃቸውን እሳቤዎችን ተግባራዊነት ለመመዘን የሚያስችል ነው፡፡
ሚኒስቴር መ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት በከፍተኛ አመራሮች የተመራ የክትትልና ድጋፍ ቡድን በ10 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ምልከታ ማድረጉን ያስታወሱት ክብርት ነቢሃ የታዩ ክፍተቶችን መሠረት በማድረግ ለክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ለዘርፍ ቢሮ ኃላፊዎች በተሰጠው ግብረ-መልስ መሰረት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ዕቅዳቸውን ከልሰው ወደ ተግባር መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡
ቴክኒካል ባለሙያዎችን ያካተተው የአሁኑ የመስክ ምልከታ ዋና ዓላማ በአመራር ደረጃ በቸካሄደው የድጋፍና ክትትል ሥራ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የገቡትን ቁርጠኝነትና የጀመሩትን የሥራ አፈጻጸም በተጠናከረ መልኩ እንዲፈጽሙ የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት መሆኑም ተመላክቷል፡፡
ይህ የሱፐርቪዥን ቡድን በየክልሎቹ ከሚገኙ አቻ የቴክኒክ ቡድኖች ጋር በቅንጅት በመሥራት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በክህሎት ልማትና በኢንዱስትሪ ሰላም ዙሪያ ያሉ ተግዳሮቶችን በቦታው በመገኘት የሚፈታና የልምድ ልውውጥ የሚያደርግ ይሆናል።
በመሆኑም በየደረጃው የሚመለከታቸው አካላት ለክትትልና ድጋፍ ቡድኑ አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ፣ የዘርፉን ሥራዎች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉ ክብርት ነቢሃ ጥሪ አቅርበዋል።

Read More Âť
News

የቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት አዲስ ተስፋ…

የቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት አዲስ ተስፋ ይዞ እንደሚመጣ የሚጠበቀው ስምምነት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም የሆነው የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ጋር በሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት የትምህርት ዘርፍ ያለውን አቅም ለማጠናከር እና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚያስችለውን የጋራ የትብብር ስምምነት ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት በትምህርት ላይ ብቻ ሳይወሰን በሰሜን ጎንደር ዞን የሚገኙ የበለጸጉ የቱሪስት መስህቦችን በተለይም የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን የቱሪዝም ሀብቶች በዘላቂነት ለማልማትና ለማስተዋወቅ የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት በቴክኒክና በዕውቀት ለመደገፍ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ባለሙያዎች ለስምምነቱ መሳካት ላሳዩት ቁርጠኝነት የዩኒቨርሲቲው አመራር ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ ይህ አጋርነት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በዕውቀትና በክህሎት የሚመራ ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት በሚደረገው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ስምምነት ተቋማቱ ያላቸውን አቅም በማቀናጀት ለሀገሪቱ የቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት አዲስ ተስፋ ይዞ እንደሚመጣም ይጠበቃል።

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top