Mols.gov.et

News

News

የሥራ ባህል ግንባታ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት

የሥራ ባህል ግንባታ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን የኩባንያዎች መፈልፈያ ለማድረግ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተቀረፀውን አዲሱን የሪፎርም እሳቤ መነሻ በማድረግ በርካታ የሥልጠና ተቋማት ኢንተርፕራይዞችን እያቋቋሙ ይገኛሉ፡፡
ኢንተርፕራይዞቹ ሰልጣኞች ተግባራዊ ሥልጠናን በተጨባጭ የሚያገኙባቸው እንደመሆናቸው ጠንካራ የሥራ ባህል ከማዳበር አንፃርም ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የሥራ ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ሸዋቀና ወልደ አማኑኤል እንደሚያብራሩት ኢንተርፕራይዞች ውስጥ የሚሳተፉ ሰልጣኞች የጊዜ አጠቃቀምን፣ ሥራን በአግባቡ መፈፀምን፣ እንዲሁም ኃላፊነትና ተጠያቂነትን በተግባር ይለማመዳሉ።
ይህም በሥራ ቦታ የሚፈለገውን የዳበረ ሥነ-ምግባር እንዲያጎለብቱ ከመርዳቱም በላይ በቡድን የመስራት፣ የመግባባትና የመተባበር ክህሎታቸው እንዲያድግ ያደርጋል። እነዚህ እሴቶች ሰልጣኞች ወደፊት ወደ ሥራው ዓለም ሲሰማሩ በቀላሉ እንዲላመዱና ውጤታማ እንዲሆኑ መሰረት ይጥላሉ።
በተጨማሪም በተቋማቱ ውስጥ የሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች የሰልጣኞችን የኢንተርፕርነርሽፕ አስተሳሰብ (Entrepreneurial mindset) በማሳደግ ረገድ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አቶ ሸዋቀና ገልጸዋል።
ሰልጣኞች የገቢና ወጪ ቁጥጥርን እንዲሁም የገበያ ትስስርን በተግባር እንዲያውቁ በማድረግ የራሳቸውን ሥራ ለመፍጠር ያላቸውን ተነሳሽነትና በራስ መተማመን ይጨምራል። ይህም ጥራትን የጠበቀ ምርትና አገልግሎት ላይ በማተኮር በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ የመሆን አቅምን ይፈጥርላቸዋል።
ባጠቃላይ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ ኢንተርፕራይዞችን ማቋቋም ሰልጣኞችን ከንድፈ-ሀሳብ ባለፈ ለተግባራዊ ዓለም የሚያዘጋጅ ስትራቴጂ ነው።
ይህ አሰራር ሰልጣኞች በሙያዊ ክህሎት የበለፀጉ፣ ኃላፊነት የሚሰማቸውና የሥራ ዲሲፕሊን የተላበሱ እንዲሆኑ በማድረግ ወደ ሥራ ገበያው ሲገቡ የተሻለ ተመራጭነት እንዲኖራቸው ትልቅ ፋይዳ እንዳለው መሪ ሥራ አስፈጻሚው አብራርተዋል፡፡

Read More »
News

የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱ ስራ ፈላጊዎችን ከቀጣሪዎች ጋር

የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱ ስራ ፈላጊዎችን ከቀጣሪዎች ጋር በማገናኘት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ስራ ፈላጊዎችን ከቀጣሪዎች ጋር በማገናኘት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የዲጂታል ሥርዓቱን ተደራሽነት ከማስፋቱም በላይ በፋይናንስ ቴክኖሎጂ አማካይነት አዳዲስ የሥራ አማራጮች እንዲፈጠሩ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የሰው ኃይል ፍላጎትና አቅርቦትን ለማጣጣም የተዘጋጀ ዲጂታል መድረክ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የሥራ ፈላጊዎች ቁጥር እና በየዘርፉ ያሉ ክፍት የሥራ መደቦችን በአንድ ማዕከል የማሰባሰብና የሰው ኃይሉን በዘመናዊ መረጃና ክህሎት በመገንባት ለዓለም አቀፍ ገበያ ጭምር ብቁ ማድረግ ከገበያ መረጃ ስርዓቱ ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ስራ ፈላጊዎችን ከቀጣሪዎች ጋር በማገናኘት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
ስርዓቱ ተግባራዊ ከተደረገ ከአራት ዓመታት በላይ እንደሆነው አንስተው፤ በዚህም ለአንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን ዜጎች በውጭ ሀገራት ስራ መሰማራታቸውን አስታውቀዋል፡።
በሀገር አቀፍ ደረጃም 45 ሺህ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ስራ ፈላጊ ወጣቶች ስራ ቅጥር እንዲፈጽሙ ስርዓቱ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን አንስተዋል።
እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፣ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የዲጂታል ሥርዓቱን ተደራሽነት ከማስፋቱም በላይ በፋይናንሻል ቴክኖሎጂ አማካይነት አዳዲስ የሥራ አማራጮች እንዲፈጠሩ ረድቷል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የዲጂታል ፕላትፎርምን በመጠቀም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን አንስተው፤ ይህንንም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በአጠቃላይ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱ በውጭ ሀገራት የርቀትና የፍሪላንስ የስራ አማራጮች እንዲሁም በአገር ውስጥ በቴክኖሎጂ የታገዙ የስራ አማራጮች ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎች ቁጥር እንዲያድግ እያስቻለ መሆኑን አመልክተዋል። ዘገባው የኢዜአ ነው።

Read More »
News

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት እና የብራዚል..

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት እና የብራዚል-ኢትዮጵያ የንግድ ምክር ቤት ስትራቴጂያዊ አጋርነት መሰረቱ
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርና የኢንዱስትሪ ክህሎት ክፍተቶችን በዓለም አቀፍ ትብብር ለመሙላት ከብራዚል ከፍተኛ ተወካዮች ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን አስታወቀ።
ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለተሟላ አጋርነትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑ ተመላክቷል።
የብራዚል የክብር ቆንስላ ክቡር ልዊዝ ፈርናንዶ ዳ ሮቻ እና የብራዚል-ኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ዶክተር ሮናልዶ ፔሬራ ባሬቶን ያካተተው ልዑካን ቡድን፤የኢንስቲትዩቱን የሥራ ማዕቀፍ፣ ስኬቶችንና በቀጣይ የጋራ ትኩረት በሚሹ ዘርፎች ላይ ከኢኒስቲትዩቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቢሩክ የልዑካን ቡድኑ ላሳየው ንቁ ተሳትፎ ምስጋናቸውን ገልጸው፣ የቀረቡትን የትብብር መስኮች በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ዶክተር ሮናልዶ ባሬቶ በበኩላቸው፣ በብራዚልና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የቆየ ትብብር መሠረት በማድረግ፣ በሥልጠና የታገዘ የኢንዱስትሪ ሽግግርን በማምጣት ዘላቂ የሰው ኃይል ልማትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሁለቱ ወገኖች መካከል የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ (MoU) የሚከተሉትን ስልታዊ የትብብር መስኮች ያካተተ ይሆናል፦
ስምምነቱ በዋነኛነት ለኢትዮጵያ አሰልጣኞች የ”አሰልጣኞች ሥልጠና” ለማስጠት፣ ሁለትዮሽ ቴክኒካል የልምድ ልውውጦችን፣ አጭር ጊዜ የኢንዱስትሪ ሥልጠናዎችና የፒኤችዲ (PhD) ፕሮግራሞች፣ የጋራ ሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትን የሚመለከቱ ፕሮግራሞች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡፡
በዚህ አጋርነት ስድስት ቅድሚያ የሚሰጣቸው የሥልጠና ዘርፎች የተለዩ ሲሆን፤ እነሱም ሜካኒካል ጥገና፣ የኢንዱስትሪ መሣሪያዎችና ማሽነሪዎች፣ የነዳጅና ጋዝ፣ ማዕድንና ማቀነባበር፣ ኤሌክትሪካልና ኦቶሜሽን ሲስተም እንዲሁም ብየዳና ፋብሪኬሽን ናቸው።

Read More »
News

ስምንት መቶ ሺህ የገጠር ወጣቶች ተጠቃሚ…

ስምንት መቶ ሺህ የገጠር ወጣቶች ተጠቃሚ የሚያደርገው ራዕይ 2 (RAYEE II) ፕሮግራም ወደ ትግበራ ሊገባ ነው
በኢትዮጵያ በገጠር ለሚገኙ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተግባራዊ የሚደረገው ራዕይ 2 (RAYEE II) ፕሮገራም የከፍተኛ አመራር የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት ተካሄዷል፡፡
መንግስት ከማስተርካርድ ፋውንዴሽንና ከኤስ ኤን ቪ(SNV) ጋር በመተባበር የሚተገብረው ይህ ፕሮግራም፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ 800 ሺህ ለሚሆኑ የገጠር ወጣቶች ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር ያለመ ነው።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታና የፕሮግራም አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ በመክፈቻ ንግግራቸው ፣ ራዕይ 2 (RAYEE II) ፕሮግራም 90 በመቶ ተጠቃሚዎች ሴቶች መሆናቸውን ገልጸው ከመደበኛ የሥራ ዕድል ፈጠራ ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ስር የሰደዱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍና ተጠቃሚነታቸው ለማረጋገጥ የተነደፈ ነው ብለዋል።
አክለውም ፕሮግራሙ ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ ከሀገራዊ የልማት ግቦች ጋር ተሳስሮ ይፈጸማል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በተለይም የሀገርን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ተግባራዊ እየተደረገ ከሚገኘው የሌማት ቱሩፋት ( በዶሮ እርባታ፣ በወተትና በአትክልትና ፍራፍሬ) ዘርፎች ጋር በማስተሳሰር ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር እንዲሁም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ የሚመሩት ይህ ፕሮግራም፣ በሰባት የሀገሪቱ ክልሎች ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
በፌዴራል ደረጃ የተቋቋመውና በከፍተኛ አመራር ደረጃ የሚመራው ይህ ስትሪንግ ኮሚቴም በቀጣይነተ በአተገባበር ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችን እየገመገመና እየፈታ ይሄዳል ተብሏል፡፡
በመጀመሪያው ምዕራፍ (Phase I) ከ278 ሺህ በላይ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር የቻለው ራዕይ (RAYEE)፣ አሁን በሁለተኛው ምዕራፍ በላቀ በጀትና ስትራቴጂ የኢትዮጵያን የገጠር ኢኮኖሚ ማነቃቃት እንደሚያስችል ተጠቁሟል፡፡

Read More »
News

የኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ለሀገር ብልጽግና…

“የኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ለሀገር ብልጽግና”፦ ታላቁ አውደ ርዕይ በመስቀል አደባባይ በደመቀ ሁኔታ ተከፈተ!
የመዲናችን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆኑት ኢንተርፕራይዞች የሥራ ውጤታቸውን ይዘው አደባባይ ወጥተዋል! በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት የሚካሄደውና ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆየው ዓመታዊ የኢንተርፕራይዞች ሳምንት አውደ ርዕይና ባዛር በመስቀል አደባባይ በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በመክፈቻው ላይ እንደገለጹት፣ መንግስት የሰው ኃይልን ወደ ምርታማነት ለመቀየር ባደረገው ጥረት ባለፉት ዓመታት ብቻ ከ2 ሚሊዮን በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በበኩላቸው፣ ዘርፉ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና ለኢንዱስትሪ ሽግግር ያለውን ፋይዳ አብራርተዋል። ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ብቻ ለ11,605 ኢንተርፕራይዞች ከ13.5 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩንም አስታውቀዋል፡፡
በተመሳሳይ ለ5,983 አንቀሳቃሾች 2.8 ቢሊዮን ብር ብድር የቀረበ ሲሆን፣ ለ1,571 ኢንተርፕራይዞች የ706.3 ሚሊዮን ብር የመሣሪያ ሊዝ ድጋፍ ተደርጓል። 10,921 ኢንተርፕራይዞች ደግሞ ከጥቃቅን ወደ አነስተኛ ደረጃ መሸጋገራቸው በመድረኩ ተገልጿል፡፡

Read More »
News

ከአሰልቺ አሠራር ወደ ቀልጣፋው የአገልግሎት ማዕከል(መሶብ)

ከአሰልቺ አሠራር ወደ ቀልጣፋው የአገልግሎት ማዕከል(መሶብ)
የሥራ ባህል ለውጥ በሀገራችን ኢትዮጵያ ፕሮጀክቶች ጀምሮ በመጨረስ እና የመንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት በማዘመን ሂደት እየተገለጠ ይገኛል፡፡
ከልማት ፕሮጀክቶች አኳያ በኮሪደር ልማትና በሌሎችም ግንባታዎች ላይ የምናየው የቀንና ሌሊት ትጋት፣ ሥራን የዜግነት ክብር አድርጎ የማየት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ያሳያል። በተመሳሳይ መንግስት ዜጎችን ከእንግልት ለማዳን በመሶብ አንድ ማዕከል ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለዜጎች በማቅረብ ረገድ አርአያ የሚሆን ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎታቸውን እያቀረቡ ከሚገኙ ተቋማት መካከል ደግሞ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠቃሽ ነው፡፡ ሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ዜጎች የሥራ ፈቃድ እድሳት እና ክሊራንስ የመሳሰሉ አገልግሎቶች እየሰጠ ይገኛል፡፡
በተመሳሳይ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተለያዩ የሥራና ክህሎት ቢሮ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ አስገብተው ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽ ከተደረገባቸው ክልሎች አንዱ የሆነው የሲዳማ ክልል በማዕከሉ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች የኢንተርፕራይዝ ምዝገባ እና የሥራ ምዝገባ ይገኙበታል፡፡ በዚህም ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ መሆኑ የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ ገልጸዋል፡፡
የሥራ ባህል ምንነት በዋናነት የሚለካው ለተገልጋይ በሚሰጥ ክብርና ለጊዜ በሚሰጥ ዋጋ ነው ያሚሉት አቶ ከፍ ያለው ቀደም ሲል አንድ ዜጋ የሥራ ምዝገባ፣ ንግድ ለመጀመር ወይም ልዩ ልዩ ፈቃዶችን ለማግኘት በየመሥሪያ ቤቱ ሲንከራተትና ሲንገላታ ይስተዋል ነበር። አሁን ግን የመሶብ አንድ ማዕከል ይህንን እንግልት በማስቀረት ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር እንዲያገኙ አስችሏል ብለዋል።
እንደ አቶ ከፍያለው ገለጻ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት በማድረግ አዲስ የሥራ ባህል መፍጠር አስችሏል።
አገልግሎቱ ተደራሽ በሆነባቸው አካባቢዎች እንደ ኮሪደር ልማቱ ሁሉ፣ በመሶብ ማዕከላትም የሚታየው ቁርጠኝነት አገልግሎቶች በተቀመጠላቸው የሰዓት ገደብ (Service Level Agreement) እንዲጠናቀቁ ከማድረጉም በላይ የመንግሥት ሠራተኛው ለዜጎች ያለውን አገልጋይነትና ለሥራው ያለውን ታማኝነት በተግባር የሚያሳይበት መድረክ ሆኗል።
አንድ ፕሮጀክት በወቅቱ ሲጠናቀቅ ሀገር እንደምታተርፈው ሁሉ፣ አንድ ዜጋ አገልግሎትን ያለ እንግልት ሲያገኝም ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል። እንግልት ሲቀንስ ዜጋው ጊዜውንና ጉልበቱን ምርታማነት ላይ ያውላል።
መሶብ አንድ ማዕከል ይህንን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር፣ ዜጎች በሀገራቸው የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና በኢኮኖሚው ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማድረጉን ቀጥሏል።

Read More »
News

“የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን በማጠናከር ረገድ …

“የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን በማጠናከር ረገድ ስኬታማ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው”፤
የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት
በሀገራችን የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን (Entrepreneurship Ecosystem) በማጠናከርና ወጣቶች ወደ ሥራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ አዳዲስ የንግድ ሐሳቦችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ስልታዊ ድጋፎችን እያከናወነ ይገኛል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሀሰን ሁሴን እንደገለጹት፤ ተቋማወጣቶች የራሳቸውን የፈጠራ ሐሳብ ይዘው ሲመጡ፣ ያ ሐሳብ ወደ ውጤታማ ኢንተርፕራይዝ እንዲያድግ የሚያስችል የክህሎት፣ የማማከርና የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት ላይ ነው።
ዶክተር ሀሰን አክለውም፣ ከክህሎት ድጋፍ በተጨማሪ የገበያና የፋይናንስ ትስስር ለሥራ ፈጣሪዎች ስኬታማነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ከባንኮችና ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ለፈጣሪዎች የብድርና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን የማመቻቸት ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
አሁን ላይ በገበያ ውስጥ የሚታዩ ስኬታማ ስታርታፖች የኢንስቲትዩቱ ስልታዊ ድጋፍ ውጤቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ወጣቶች ያላቸውን የፈጠራ አቅም በመጠቀም ወደ ሥራ ፈጣሪነት እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ የኢንተርፕረነርሽፕ ንቅናቄ በሀገራችን ያለውን የሥራ አጥነት ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የኢኮኖሚ ዕድገቱን ለማፋጠን እንደ ትልቅ መፍትሔ የሚወሰድ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።

Read More »
News

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ እና የሀብት መፍጠሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል
በድሬዳዋ ከተማ ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን በአዲሱ የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ እንዲሁም የመሰረታዊ ክህሎት (Basic skill modules) ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ።
ይህ አዲስ ስትራቴጂ ‹‹ከስልጠና በላይ›› በሚል መሪ ቃል የተቀረጸ ሲሆን ዋና ዓላማውም የሰልጣኞችን የአስተሳሰብ አድማስ በማስፋት ተቋማት የችግር ፈቺ መፍትሄዎች ምንጭ እና የሀብት መፍጠሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል ነው።
ስትራቴጂው በተለይም በፋብሪኬሽን ኢንጅነሪንግ እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ነጻነትን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የስልጠናው ይዘት በዋናነት አራት ስትራቴጂካዊ የትኩረት መስኮችን የተከተለ ሲሆን እነሱም የዘርፉን አስተዳደር ማጎልበት፣ የስልጠናውን አግባብነትና ጥራት ማረጋገጥ፣ ሰልጣኞችን ለሥራ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎቶችን ማስታጠቅ እንዲሁም ምርምርና ፈጠራን ማበረታታት ናቸው።
ስልጠናው ገበያ መር መሆኑ የሥራ ገበያው የማይፈልገውን ሙያ በማሰልጠን የሚባክነውን ሀብትና የሚፈጠረውን ሥራ አጥነት ለመቀነስ እንደሚያስገድድ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ውስጥ የተቀረጹ አምስት መሰረታዊ የክህሎት ሞጁሎች ለአሰልጣኞቹ ቀርበዋል።
አነዚህም ልል ክህሎቶች (Soft Skills) ፣ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎቶች፣ ስነ-ምግባርና ዜጋዊ ኃላፊነት፣ የሥራ ፈጣሪነት አስተሳሰብን ማሳደግ እንዲሁም የንግድ ሥራዎችን መንደፍና ማስጀመር የሚሉ ናቸው።
እነዚህ ሞጁሎች ሰልጣኞች ከመደበኛው የተግባር ስልጠና በተጨማሪ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሥራ ዓለም ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን ሁለንተናዊ ብቃት እንዲላበሱ ለማድረግ ታስበው የተዘጋጁ መሆኑ ተጠቅሷል።

Read More »
News

ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም ያለው የቱሪዝም ዘርፍ

ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም ያለው የቱሪዝም ዘርፍ
የቱሪዝም ዘርፍ ያለውን ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ እምቅ አቅም መነሻ በማድረግ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስልጠናዎችን በተቀናጀ መልኩ እየሠጠ እንደሚገኝ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ኢንስቲትዩቱ የሥራ አጥነትን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍና የኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስልታዊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
የኢንስቲትዩቱ የምርምርና ማማከር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም እንደገለጹት፤ የቱሪዝም ዘርፍ በባህሪው ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ፣ ኢንስቲትዩቱ የሚሰጣቸው ስልጠናዎች ከገበያው ተጨባጭ ፍላጎት ጋር እንዲጣጣሙ እየተደረገ ነው።
በተለይም ወጣቶች በዘርፉ ሰልጥነው ሲወጡ የራሳቸውን ቢዝነስ እንዲጀምሩ የሚያስችል የክህሎትና የሥራ ፈጠራ ስልጠናዎችን በማቀናጀት፣ ዜጎች መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎችም የሥራ ዕድል የሚፈጥሩበት ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ይታሰብ አክለውም፣ አሁን ላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱ አዳዲስ የቱሪዝም ቴክኖሎጂዎችን በስልጠና ክፍሎቹ በማስተዋወቅ ሰልጣኞች በዘመናዊ መንገድ አገልግሎት መስጠት የሚችሉበትን ብቃት እንዲላበሱ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

Read More »
News

“ከፈጠራ ሐሳብ ወደ ተጨባጭ ተግባር’’

“ከፈጠራ ሐሳብ ወደ ተጨባጭ ተግባር’’
የክህሎት ባንክ የሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን ችግር ፈቺ ተግባር በማሸጋገር ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለፀ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም በሆነው በኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘው “የክህሎት ባንክ” (Skill Bank)፣ የፈጠራ ስራዎችን በማልማትና ወደ ንግድ ማዕቀፍ (Commercialization) በማሸጋገር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
ማዕከሉ በተለይ በክረምት መርሃ-ግብር እና በ“ስኪል ኢትዮጵያ ስታርታፕ” ፕሮግራም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ለገበያ በማቅረብ ለሀገራዊ ምርታማነት የላቀ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ነው፡፡
የኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂና ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፀዳለ ተክሉ እንደገለጹት፤ ስኪል ባንክ ከመረጃ ቋትነት ባለፈ አዳዲስ የፈጠራ ሐሳቦች ተቀርጸው ወደ ተግባር የሚቀየሩበት ህያው የፈጠራ መድረክ (Innovation Hub) ነው ።
እስካሁንም ከ600 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ160 በላይ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲፈጠሩ ያደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በርካታ ተኪ ቴክኖሎጂዎች ወደ ተጠቃሚው ማህበረሰብ እየደረሱ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ወይዘሮ ፀዳለ ገለጻ፣ በማዕከሉ ከለሙና ወደ ንግድ ከተሸጋገሩ ስኬታማ ቴክኖሎጂዎች መካከል በኢንተርኔት የታገዘ ስማርት መስኖ (IoT Smart Irrigation) በአፋርና ሶማሌ ክልሎች በንግድ ደረጃ ሥራ ላይ የዋለ ሲሆን፣ አፈር አልባ የሆነው የ”ሃይድሮፖኒክ” የእንስሳት መኖ ማምረቻ ቴክኖሎጂም ከኢንተርፕራይዞች ጋር በተፈጠረ ትስስር ምርቱን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
tigTIG
Scroll to Top