Mols.gov.et

mols mols

News

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር …

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ማብቃትና ማሰማራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአቪዬሽን ዘርፍ የሰው ኃይል አቅርቦት፣ ስልጠና እና ስምሪት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ የኢትዮጵያ ወጣቶች በዘርፉ አሰልጥኖ ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁ አድርጎ ማቅረብ የሚያስችል ነው።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ እንደገለጹት፣ ስምምነቱ የከባተ ልምድ ያለውን የኢትዮጵያ የአየር መንገድ ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ በሌሎችም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለአቬሽን ዘርፉ ብቁ ወጣቶችን አሰልጥኖ ለሀገር ውስጥና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ በቀለ ባይ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ በዓመት ከ3 ሺህ እስከ 4 ሺህ የሚደርስ አዲስ ሠራተኛ እንደሚቀጥር ጠቁመዋል።
ሰራተኞችን የመመልመል እና የማሰልጠን ሂደት አድካሚና ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር መሥራት የሥራ ድግግሞሽን ከማስቀረቱም በላይ የሀገሪቱን ወጣቶች በአግባቡ በማብቃት ተወዳዳሪ ዜጎችን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ከኮቪድ-19 በኋላ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአቪዬሽን ባለሙያዎች እጥረት እንዳለ የገለጹት ኃላፊው ይህንን ክፍተት ለመሙላት በቂ እና ብቁ ወጣቶችን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በትብብር እና በቅንጅት ማሰልጥን ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ገልጸዋል፡፡
በዚህ ስልጠና የሚያልፉ ወጣቶች በዋናነት ለኢትያጵያ አየር መንገድና ለሌሎችም ሀገራት አቬየሽን የማቅረብ ሥራ በስፋት እንደሚሠራ ጠቁመዋል፡፡
ይህ ስምምነት የዜጎችን ሙያዊ ብቃት በማጎልበት በማሳደግ፣ በየትኛውም የዓለም ብቁ ተወዳዳሪ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲሰሩ ያስችላል ተብሏል፡፡
በቀጣይም የመግባቢያ ስምምነቱ ወደ ዝርዝር ዕቅድ ተቀይሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር እንደሚገባ ተገልጿል።

Read More »
News

ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል

ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል
የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ስትሪንግ ኮሚቴ ዕቅድ አፈፃፀሙን ክቡር አምባሳደር አምባሳደር ግርማ ብሩን ጨምሮ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገምግሟል፡፡
በዚህም ባለፉት ሰባት ወራት ከ447 ሺህ በላይ ዜጎችን ጥራት ያለው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ በመድረኩ ተጠቁሟል፡፡
በመድረኩ ላይ እንደተመለከተው፣ የተመዘገበው ስኬት የሰው ኃይል ዝግጅትን፣ የሥራ ገበያ ፍላጎትንና ለሥራው ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርን ማዕከል ባደረገ የጋራ ዕቅድ ሁሉም ባለድርሻና አስፈፃሚ አካላት ተሰናስለው በመስራታቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ይህ የተቀናጀ አሠራር የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ባለፉት ሰባት ወራት በተተከናወኑ ሥራዎች የተገኘው ውጤት፤ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ መሻሻል የታየበት መሆኑ ተመላክቷል።
በቀጣይም በሰው ኃይል ዝግጅት ረገድ የግል ዘርፉና ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸው ድርጅቶች በስፋት እንዲሳተፉ ማበረታታት እንደሚገባ ተመላክቷል።
ይህም የዜጎችን ተወዳዳሪነትና የሥራ ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ መሆኑና የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎችን በላቀ ትጋት ማጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡

Read More »
News

በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ …

በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጨባጭ፣ ተስፋ ሰጪና አዳጊ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል
በሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ ያለውን ውዝፍ፣ አሁናዊ እና የመጪውን ጊዜ ሀገራዊ ፍላጎት መመለስ በዘርፉ ተግባራዊ የተደረገው ፎርም ዋና ማጠንጠኛ ነው።
በዚህ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተቀርፆ ወደ ሥራ እንዲገባ የተደረገው “ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ” ስትራቴጂ፣ ዛሬ ላይ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስነምዳር ውስጥ ተጨባጭ፣ ተስፋ ሰጪና አዳጊ ውጤቶችን ማስመዝገብ ችሏል።
በያዝነው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ፣ ከ2.6 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል።
የሥራ ዕድል ፈጠራውን በዘርፍ ስንመለከተው፤ የአገልግሎት ዘርፉ የ40.5 በመቶ ድርሻ በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲመራ፣ የግብርናው ዘርፍ 37.5 በመቶ እና ቀሪው 22 በመቶ የሚሆነው የሥራ ዕድል በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተፈጠረ ነው።
ከተፈጠረው አጠቃላይ የሥራ ዕድል ውስጥም 53 በመቶው በከተማ አካባቢዎች ሲሆን፣ ቀሪው 47 በመቶው ደግሞ በገጠር ለሚኖሩ ዜጎች የተመቻቸ ነው። ይህ ስርጭት በከተማም ሆነ በገጠር የሚገኙ ሥራ ፈላጊዎችን ተደራሽ ለማድረግ በመንግስት የተሰጠውን ልዩ ትኩረት ማሳያ ነው።
የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን በፈጠራና በፍትነት በማከናወን ከዕድገት ተኮር ዘርፎች ጋር ለማስተሳሰር በየደረጃው የተደረገው ሁሉን አቀፍ ጥረትና ርብርብ፣ ለዚህ ታላቅ ውጤት መገኘት የአንበሳውን ድርሻ ተጫውቷል።
ለዜጎች ሰፋፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳደግና የኢንተርፕሪነርሺፕ ምህዳሩን በማስፋት፣ ዜጎች የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚደረገው ድጋፍ፤ የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ ለሀገራዊው የድህነት ቅነሳ ጉዞ ያለው ፋይዳ የጎላ ነው።

Read More »
News

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚካሄደው ድጋፍና ክትትል …

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚካሄደው ድጋፍና ክትትል የዜጎችን ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ተገለፀ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በአማራ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ የተከናወኑ የሥራና ሥራ ሥምሪት፣ የክህሎት ልማት፣ የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳዮች እና የተቋም ግንባታ ተግባራትን ላይ ጠለቅ ያለ የመስክ ምልከታ አካሂዷል፡፡
የድጋፍና ክትትል ቡድኑን የመሩት የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ አዝመራ ከበደ፤ በክልሉ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው አበረታች ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን መመልከት ችለናል ብለዋል፡፡
በክልሉ በክህሎት ልማት ዘርፍ የተቀረጹ አዳዲስ እሳቤዎች ወደ ተግባር ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አድንቀው በተለይ ኢንተርፕራይዞች ለመደገፍ የሚደረገው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ሥራ፣ በተጨባጭ ውጤት እየታየበት መሆኑ በመስክ ምልከታው መረጋገጡን ጠቁመዋል።
ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር በኮሪደር ልማት እና በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቮች ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ በአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ የተቀረጹ እሳቤዎች ወደ መሬት ለማውረድ የተጀመሩ ጥረቶች አሰሪም ሰራተኛውም ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡
ቡድኑ በቆይታው ጠንካራ ጎኖችን ተጠናክረው አንዲቀጥሉ ከማበረታታት ባለፈ፣ በሂደቱ የታዩ ክፍተቶች እንዲታረሙና ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አመላክቷል፡፡
ይህ የድጋፍና ክትትል ሥራ በክልሉ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑና የዜጎችን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ በሚያስችል መንግድ ለመተግበር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆንም የክልሉ የዘርፉ ኃለፊዎች ገልጸዋል።

Read More »
News

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን …

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ ነው – ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ 11ኛውን የሕብረት የስምምነት ተፈራርመዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
‎‎
የአሠሪና ሠራተኛ መልካም ግንኙነት መኖሩ ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዋነኛው መሣሪያ መሆኑንም አፅንዖት አንስተዋል።
‎በዕለቱ የተፈረመው የሕብረት ስምምነትም በአየር መንገዱ አመራርና በሠራተኛው መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥና ለተቋሙ ዘላቂ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አመላክተዋል፡፡

ይህ ዓይነቱ ስምምነት በሚኒስቴሩ የታለመውን ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት የመገንባት ራዕይ በተግባር የሚያሳይ ሲሉም ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የሕብረት ስምምነቱ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ቀጣይነት ያለው ስኬት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልፀዋል።
የሕብረት ስምምነቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዕድገት በማፋጠን የሠራተኞችን ጥቅም በዘላቂነት የሚያስከብር መሆኑንም አብራርተዋል።

Read More »
News

ስምምነቱ በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት…

ስምምነቱ በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ኢንስቲትዩቱ አስታወቀ
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር፤ ስምምነቱ ኢንስቲትዩቱ ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ጋር የተያያዙ ስልጠናዎችን በማሻሻል በኩል ትርጉም ያለው ስራ እንዲሰራ ዕድል የሚፈጥርና በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ገልፀዋል።
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን የሚፈቱ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎች በኢንስቲትዩቱ እንደሚሰሩም አመላክተዋል።
ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ችግር ፈቺ የሆኑ ተኪ ቴክኖሎጂዎችን የመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራት በትኩረት እንደሚከናወንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በበኩላቸው፤ የቡና ጥራትን በመጠበቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የክህሎት ስልጠናዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ ካለው የማሰልጠን፣ የፈጠራ እና የምርምር ሥራዎች አቅም አንጻር አብሮ መስራቱ ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ የያዛቸውን ዕቅዶች ለማሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆንም ነው ያመላከቱት። መረጃው የኢኒስቲትዪቱ ነው።

Read More »
News

የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ተጠቀሚ መሆን ጀመሩ!

የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ተጠቀሚ መሆን ጀመሩ!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከ200ሺ በላይ ወጣቶች እና የመንግስት ስራተኞች ተመዝግበው ከ157ሺ በላይ ዜጎች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መውሰዳቸውን ተገለፀ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተጀመረው የ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች የዲጂታል ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩንም አብራርተዋል።
ሰልጣኞች የብቃት ማረጋገጫ ከማግኘት ባለፈ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማካኝነት የሥራ እድል ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውንም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂን ለማሳካት ሀገራችን የምታደርገው ጉዞ አካል ሲሆን በሦስት ኣመታት ውስጥ ሀገራችንን በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ ማድረግ የሚችሉ 5ሚሊዮን ሰዎችን ማብቃትን ዓላማው አድርጎ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

Read More »
News

የሰው ልጅን የፈጠራ ችሎታ ከቴክኖሎጂ ጋር ማጣመር

የሰው ልጅን የፈጠራ ችሎታ ከቴክኖሎጂ ጋር ማጣመር
የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሳምንታዊ የጥናትና ምርምር ሴሚናር ከጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ጋር በተያያዘ በአራተኛው (4.0) እና በአምስተኛው(5.0) የኢንዱስትሪ አብዮቶች፣ በኢንዱስትሪ ሽግግርና በምዘና ሥርዓት ውጤታማነት ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ሪፖርት እና ዕቅድ ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመድረኩ ላይ የቀረበው የመጀመሪያው የጥናት ሪፖርት እንደሚያመለክተው ዓለም አቀፉ የኢንዱስትሪ አብዮት ከዲጂታላይዜሽን እና ከአውቶሜሽን ባለፈ የሰውን ልጅ የፈጠራ ችሎታ ከማሽኖች ጥምረት ጋር ወደሚያገናኘው አዲሱ ኢንዱስትሪ አብዮት 5.0 እየተሸጋገረ ይገኛል። ይህ ለውጥ በተለይም በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ዘርፍ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች አዳዲስና ዘመናዊ የክህሎት ዓይነቶችን እንዲላበሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
አራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ማሽኖች ያለ ሰው ንክኪ እንዲግባቡና ራሳቸውን ችለው ውሳኔ እንዲሰጡ የሚያደርግ ሲሆን አምስተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ደ ደግሞ ቴክኖሎጂ የሰውን ልጅ የመፍጠር አቅም እንዲያግዝ እንጂ እንዲተካው የማይፈለግበት ሥርዓት ነው።
ይህ አዲሱ አብዮት ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም እና ኢንዱስትሪዎች በችግር ጊዜ በቀላሉ የማይወድቁበትን ጥንካሬ መገንባት ላይ ትኩረት ያደርጋል።
ሆኖም አሁን ያለው የሀገሪቱ የቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ-ትምህርት አሁንም በአራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ቴክኖሎጂዎች ላይ ገና እየተንደረደረ መሆኑና በዲጂታል ፋሽን ንድፍ፣ በስማርት ማምረቻ እና በዘላቂነት ረገድ ሰፊ የክህሎት ክፍተት መኖሩ በሪፖርቱ ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ሰልጣኞች ማሽኖችን ከማንቀሳቀስ ባለፈ የፈጠራ አስተሳሰብ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ጠንቅቀው ማወቅ እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቷል።
ለዚህም እንደ መፍትሄ የቀረቡት ምክረ-ሀሳቦች የትምህርት ሥርዓቱን ማሻሻል፣ ቴክኖሎጂ በየጊዜው የሚቀየር በመሆኑ የዕድሜ ልክ ትምህርት ግንዛቤን ማስረጽ፣ የመንግስትና የኢንዱስትሪ ትብብርን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማሽኖች ሊተኳቸው የማይችሏቸውን የሰው ልጅ ልዩ ባህሪያት (Soft Skills) ማዳበር የሚሉ ናቸው። ይህም ሰልጣኞችን ከቀጣሪነት ባለፈ የቴክኖሎጂ መሪ እና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ተብሎ ይታመናል።
በተጨማሪም በሴሚናሩ ማጠናቀቂያ ላይ በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የምዘና ልምዶች እና ምሩቃን ብቃት ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ የሚያሳይ የጥናት ዕቅድ (Proposal) ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ይህ የጥናት ዕቅድ ወደፊት በዘርፉ ላይ የሚታዩ የአፈጻጸም እና የጥራት ችግሮችን ለመፍታት እንደ ዋነኛ ግብዓት ያገለግላል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተገልጿል፡፡

Read More »
News

የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ቅንጅት..

የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ቅንጅት፤ ለተወዳዳሪ የሰው ኃይል ልማት!
ትውልድን ለመጪው ዘመን ማዘጋጀትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቱን ማረጋገጥ የጊዜው አጣዳፊ ጥያቄ ነው።
ይህ በተሟላ ደረጃ እውን እንዲሆን በትምህርትና ሥልጠና ተቋማት መካከል ያለው ቅንጅት መጠናከር የሰው ኃይል ልማታችን ከሥራ ገበያው ፍላጎት ጋር እንድናጣጣምና በሥራ ዕድል ፈጠራና በፈጠራ ሥነ-ምህዳሩ ላይ የሚኖረው አበርክቶ እንዲጎለብት ያደርጋል።
ላለፈው አንድ ዓመት በሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን የተቋም በህል ግንባታ ሥራችን አካል የሆነው ወርሃዊ “የማለዳ ውይይት” መርሃ-ግብር በዛሬው እለት በከፍተኛ ትምህርት፣ በቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ተቋማት መካከል ስትራቴጂካዊና እሴት-አካይ ቅንጅት መፍጠር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር ተካሂዷል።
ይህ መድረክ ተቋማቱ ለየብቻ ከመጓዝ ወጥተው ለጋራ ሀገራዊ ግብ እንዲሰናሰሉ የሚያስችል አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፍቷል።
በዚህም ከእውቀትና ክህሎት ባለፈ፣ ችግርን ወደ ዕድል የሚቀይሩና ሥነ-ልቦናዊ ጥንካሬ ያላቸው፤ በጠንካራ ሥነ-ምግባር የታነጹ፣ አቋራጭ መንገድን የማይሹና ለሀገራዊ ውጤት የሚተጉ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ የሚያፋጥኑና በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት የሰው ኃይል ልማታችን ዋነኛ ማጠንጠኛ መሆን ይኖርበታል፡፡
ከምክክሩ ጎን ለጎን የመድረኩ ተሣታፊዎች የኢትዮጵያን የሥራ ገበያ ሥርዓት እና የመንግስት አገልግሎት የፈጠራና የማሻሻያ ማዕከን በመጎብኘት በቀጣይ ተቀናጅቶ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተቀራርቦ ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል።

Read More »
News

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው

የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው የዘርፉ እሳቤ……
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከዚህ ቀደም የሚታወቁት በአጫጭር እና መደበኛ ፕሮግራም ያሰለጠኗቸውን ወጣቶች ሰርተፍኬት ሰጥተው በመሸኘት ነበር ፡፡ አሁን ግን ይህንን የተለመደ አሰራር የሚቀይር አዲስ እሳቤ ተቀርጾ በዘርፉ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል፡፡
እሳቤው ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸው ከሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ጋር የሚስማማ ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ የሚያስችል አዲስ እይታ ነው፡፡
በአሁን ወቀት ይህንን እሳቤ እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል፡፡ በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ 20% ቁጠባ እንዲቆጥቡ በማድረግ፣ ለሚመሰርቱት ኢንተርፕራይዝ መነሻ የሚሆን አቅም እንዲፈጥሩ እየተደረገ ይገኛል።
ከቴክኒካዊ ስልጠናው ጎን ለጎን በቀጣይ የኢንተርፕራይዝ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ስኬታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የኢንተርፕሪነርሺፕ እሳቤን ለመላበስ የሚያስችላቸውን ስልጠናም ከተቋማቱ ያገኛሉ፡፡
ኮሌጆች ያሏቸውን ማሽኖች ተጠቅመው እያመረቱ እንዲሰለጥኑ፣ እየሰለጠኑ እንዲያመርቱ የተቀመጠው አቅጣጫ ደግሞ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን ብቃትና ተወዳዳሪነት የሚያልቅ ሌላኛው የአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ገፅታ ነው፡፡
የቴክነኒክና ሙያ ተቋማት ጥራት ያለው ስልጠና አግኝተው፣ የኢንተርፕሪነርሺፕን ባህሪ ተላብሰው፣ በኮሌጆቹ ውስጥ በሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች እጃቸውን፣ ልባቸውንና አእምሯቸውን ቃኝተውና ኢንተርፕራይዝ መስርተው የሚወጡ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች የሚወጡባቸው ተቋማት ናቸው፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ዜጎች በስፋት የሚፈሩባቸው ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል፣ የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ ስብራት የሚጠግኑ ባለወርቅ እጆች የሚፈጠሩባቸውና ሀገርን የሚያልቁ ኩባንያዎች የሚፈለፈሉባቸው የፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነታቸውን ዕውን ማድረግ ደግሞ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተቀረፀው አዲሱ የክህሎት ልማት እሳቤ አዲሱ መዳረሻ ግብ ነው!

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
tigTIG
Scroll to Top