Mols.gov.et

mols admin

News

ማሳሰቢያ

ማሳሰቢያ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተግባራዊ እያደረገ ያለው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መነሻና መዳረሻው የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው፡፡
በዘርፉ ባለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት በተሰራው ጠንካራ የሪፎርም ሥራ በቴክኖሎጂ ጭምር በመታገዝ ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ ወጪና እንግልት በመታደግ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህ ሥራ አሁንም ተጠናክሮ እየቀጠለ ይገኛል፡፡
ነገር ግን ስምሪቱን በተመለከተ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ስምና አርማ እንዲሁም የከፍተኛ አመራሩን ስምና ምስል ጭምር በመጠቀም የተለያዩ ማስታወቂያዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሕገወጦች በመዘዋወር ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መሆናቸው ታውቆ ሁሉም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይዳረግ ጥንቃቄ እንዲያደረግ እናሳስባለን፡፡
የሥራ ስምሪቱን በተመለከተ አዳዲስ ነገሮች ሲኖሩ የተቋማችንን ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስርን ጨምሮ በሁሉም የሚደያ አማራጮች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልግ ማንኛው ሰው በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ (https://lmis.gov.et/auth) እንዲመዘገብ እና ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

Read More Âť
News

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ክቡር ቼን ሃይ ጋር በቅንጅት መስራት በምንችልባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ወይይት ተካሄደ፡፡

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ክቡር ቼን ሃይ ጋር በቅንጅት መስራት በምንችልባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ወይይት ተካሄደ፡፡

በውይይቱ ላይ የተገኙት ክብርት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት በቻይና እድገትና ልማት ውስጥ የቴክኒከና ሙያ ትልቅ አበርክቶ እንደነበረው እና ኢትዮጵያም ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በያዘችው ጉዞ ዘርፉ የማይተካ ሚና እንዳለው ከግምት በማስገባት መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራው ያለውን ሥራ በዝርዝር ለአምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡
በቀጣይም ቻይና ለኢትዮጵያ በዘርፉ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ክቡር አምባሳደሩ አረጋግጠውልኛል ብለዋል ፡፡
ከውይይቱ በኋላ በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በቻይና መንግስት ድጋፍ የተገነባውን የሉባን ወርክሾፕ የጎበኘን ሲሆን በቻይና መንግስት የትምህርት እድል ተሰጥቷቸው ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ያሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በበይነ መረብ አግኝተው ማናገራቸውንና ማበራታታቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህ ግንኙነት ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር የቻይና አፍሪካን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድግ በመሆኑ በኢትዮጵያ የቻይና አምበሳደር ለክቡር ቼን ሃይ በትብብር አብሮ ለመስራት ላሳዩን ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

የኮደርስ ስልጠና ዜጎች በዲጂታሉ ዓለም ባለው የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያግዛል- የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

የኮደርስ ስልጠና ዜጎች በዲጂታሉ ዓለም ባለው የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያግዛል- የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
”አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ መርኃ ግብር የዜጎችን አቅም በማሳደግ በዲጂታሉ ዓለም ባለው የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያግዛል ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የ”አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ መርኃ ግብር በኢትዮጵያ መንግስትና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ትብብር የተጀመረ የዲጂታል ሼል ክህሎት ማሳደጊያ ፕሮጀክት ነው።
ፕሮጀክቱ “ትውልድ ይማር፣ ትውልድ ይሰልጥን፣ከዓለም ጋር ይፎካከር” በሚል እሳቤ ዜጎች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ብቁ እንዲሆኑ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ፕሮጀክቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣በአንድሮይድ ማበልፀግ ፣ በዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲጨብጡ የሚያስችል ነው።
ከዚሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የ”አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ ኢኒሼቲቭ የዜጎችን የቴክኖሎጂ ተወዳዳሪነት አቅም የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ዜጎች የዲጂታል ክህሎት በመጨበጥ ስራ እና ሀብትን በመፍጠር ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን የበለጠ የሚያግዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ያላቸው ወጣቶችን ከማፍራት አንጻር የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ እንደሆነም ተናግረዋል።
በዚህ ሂደት የሚያልፉ ዜጎች ራሳቸውን በቴክኖሎጂ ከማብቃት በተጨማሪ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ማፍለቅ እንደሚችሉ ነው የተናገሩት።
ስልጠናው በሌላው ዓለም ያሉ ስራዎችን ባሉበት ሆነው መስራት እንዲችሉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።
ከዚህም ባለፈ የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ፈጠራ ለሀገር ለማበርከት እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ሲሉ አመላክተዋል።
ይህም የዜጎችን የተወዳዳሪነት አቅም በማሳደግ በዲጂታሉ ዓለም ባለው የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያግዛል ነው ያሉት።
መርኃ ግብሩ በፈረንጆቹ በ2026 አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታሳይንስና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት የሚያስጨብጥ ይሆናል።
#ኢዜአ
መስከረም 18/2017

Read More Âť
News

የጥራት ሥራ አመራርን በአግባቡ መተግበር የሪፎረም ሥራዎቻችንን ለማፅናት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

የጥራት ሥራ አመራርን በአግባቡ መተግበር የሪፎረም ሥራዎቻችንን ለማፅናት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እየተገበረው በሚገኘው ISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር የኦዲት ግኝት ላይ ውይይት ተካሄዷል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነቢሀ መሀመድ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት፣ ISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራርን ለመተግበር የሚያስችሉ ሥራዎች ደረጃ በደረጃ እየተከናወነ ቆይቷል፡፡
ይህን ተከትሎ በሙከራ ደረጃ በሚኒስቴር መ/ቤቱ እየተተገበረ የሚገኘውን ISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራርን ውጤታማነትን የሚመዝን የኦዲት ሥራ ተሰርቷል።
በኦዲት ግኝቶቹ መሰረት በቀጣይ በአስቸኳይ የማሻሻያና የእርምት እርምጃዎች ተወስደው ወደ ሙሉ ትግበራ ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎችን እየተገበረ የሚገኝ ተቋም እንደመሆኑ እነዚህን የሪፎርም ሥራዎች ለማፅናት የጥራት ሥራ አመራርን በአግባቡ መተግበር ወሳኝ መሆኑንም አመላክተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር 20 ተቋማትን ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን እንዲያሟሉ ዕቅድ ይዞ እየሰራ ቆይቷል፡፡
እስካሁን የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የISO 9001:2015 እንዲሁም የሀዋሳ ፖሊቴክኒከ ኮሌጅ የISO 21001:2018 የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አግኝተዋል፡፡

Read More Âť
News

የአሰልጣኞችን አቅም ለማሳደግ ቀጣይነት ያለው ሥራ እንደሚሰራ ተጠቆመ

የአሰልጣኞችን አቅም ለማሳደግ ቀጣይነት ያለው ሥራ እንደሚሰራ ተጠቆመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቸ “ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና አሰልጣኞች ስልጠና አጠቃላይ ሂደት ገምግመዋል፡፡
በዘርፉ ፖሊሲና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ ተቀራራቢ ግንዛቤ መፍጠር እና የአሰልጣኞችን ባህሪያዊና ቴክኒካዊ ብቃትን ማሳደግ ታሳቢ ባደረገው በዚህ የስልጠና መድረክ በ19 የስልጠና ማዕከላት ከ20 ሺህ በላይ አሰልጣኞች ተሳትፈዋል፡፡ ይህም ከዕቅዱ 86 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡
የሥልጠና መድረኩ ግቡን ያሳካና ለቀጣይ የአቅም ግንባታ ሥራዎች በርካታ ልምዶች የተገኙበት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ እንደ ዘርፍ የተቀረጹ አዳዲስ እሳቤዎችንና ሰትራቴጂዎችን ወደ መሬት ለማውረድ የአሰልጣኞች ሚና የማይተካ ነው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ መድረክ አሰልጣኞች በፖሊሲና ሰትራቴጂዎች ላይ ተቀራራቢ ግንዛቤና ዝግጁነት እንዲኖራቸው ከማድረጉም ባሻገር በዘርፉ መነቃቃትን መፍጠር ችሏል፡፡
በቀጣይ በተለያዩ ምክንያቶች ስልጠናውን መውሰድ ያልቻሉ አሰልጣኞችን ለመድረስ እንደሚሰራ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር የአሰልጣኞቸ የአቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ለመድረኩ ስኬት አበርክቶ ለነበራቸው አስተባባሪዎች፣ የክልል አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ከፍተኛ የትምህርትና የቴክኒክና ማሰልጠኛ ተቋማት አንዲሁም ለሁሉም ሰልጣኞች ክብርት ሚንስትር ምስጋና አቅርበዋል፡፡

Read More Âť
News

የክህሎት ስልጠና ለወሰዱ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር …

የክህሎት ስልጠና ለወሰዱ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ መሆኑን የሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ቢሮ ገለፀ፡፡
በቢሮው የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ም/ል ኃላፊ አቶ ካንቹላ ካንቤ እንደገለፁት ሥራ ፈላጊዎችን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኘው ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ከሚገኘው SHINTS ETP GARMENT PLC Ethiopia የተሰኘው ካምፓኒ ጋር በማስተሳሰር የሥራ ዕድል እየተፈጠረላቸው ይገኛል፡፡
በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና በሌሎችም አካባቢዎች የሥራ ልምድ ያላቸውን ብቁ ባለሙያዎች የመመዝገብና ከሐዋሳ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ብቃታቸውን የማስመዘን ሥራ በቢሮው እየተከናወነ እንደሚገኝም አቶ ካንቹላ ገልፀዋል፡፡
ቢሮው ከጋርመንት ፋብሪካው ጋር ከባለፈው በጀት ዓመት ጀምሮ ሲሠራ የቆየ ሲሆን በጋርመንት ዘርፍ ለሰለጠኑና ብቃታቸው በምዘና ለተረጋገጠ 1,217 ለሚሆኑ ባለሙያዎች በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ከቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡፡፡

Read More Âť
News

በከተማው ልማት ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘ ተቋም

በከተማው ልማት ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘ ተቋም
የምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማው ክህሎት መር አጫጭር እና መደበኛ ሥልጠናዎችን እየሰጠ የሚገኝ ተቋም ነው።
ተቋሙ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በክህሎት ልማት ዘርፍ ላይ ያደረገውን የሪፎርም ትግበራ ተከትሎ በአይሲቲ፣ በሆቴልና ቱሪዝም፣ አልባሳትና ጨርቃጨርቅ፣ በእንጨት፣ በቆዳና እና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ላይ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየተጋ ይገኛል፡፡
ኮሌጁ ከሥልጠና በላይ ባለው ተልዕኮ የሥልጠና ጥራቱን የሚያረጋግጡና የውስጥ ገቢ አቅሙን የሚያሳድጉ ተግባራት እያከናወነ ነው፡፡
በዚህም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ተኪ ምርቶችን እያመረተ ለተለያዩ የመንግስት ተቋማት ደረጃቸውን የጠበቁ የፈርኒቸር ውጤቶችን እያቀረበ ይገኛል፡፡
የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ለሚገኘው የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ዘመናዊ የቆሻሻ መጣያዎች እና ተንቀሳቃሽ የፈጣን ምግብ ማዘጋጃና መሸጫ ሱቆችን እያመረተ በማቅረብ በከተማው ልማት ላይ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
ይህም የኮሌጁ ሰልጣኞች የቴክኖሎጂ ሽግግርን ዕውን ለማድረግ ተጨማሪ አቅም እና የሥራ ባህል እንዲኖራቸው አስችሏል፡፡
በተመሳሳይ ኮሌጁ ከከተማ ውበትና እና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት እና ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በከተማው በኮሪደር ልማት አረንጓዴ ሥራዎች ላይ ለሚሳተፉ ዜጎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ላይ መሆኑን ኮሌጁ ያደረሰን መረጃ ይጠቁማል፡፡

Read More Âť
News

ግብርናን በማዘመን በዘርፉ እየታየ ያለውን ውጤት ለማላቅ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ግብርናን በማዘመን በዘርፉ እየታየ ያለውን ውጤት ለማላቅ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
ሁሉንም የግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል መርሃ ግብር በቅርቡ እንደሚጀምር ተጠቆመ
መርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት ተግባራዊ የሚያደርጉት ነው፡፡
ይህን በተመለከተ የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶችና አስፈላጊነቱ ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የግብርና ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ግርማ አመንቴን ጨምሮ የክልል ግብርና ቢሮ፣ የግብርና ኮሌጆች እንዲሁም የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ግብርናን በማዘመን በዘርፉ እየታየ ያለውን ውጤት ለማላቅ የባለሙያዎች አቅም ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡
ተግባራዊ የሚደረገው የግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎች የደረጃ ማሻሻያ ግብርና ሚኒስቴር የጀመረውን ውጤታማ ሥራ የሚያጠናክርና እየተገኘ ያለውን ውጤት በእጅጉ ከፍ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል፡፡
በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ የቴክኒክና ሙያ ስርዓቱ እስከ ደረጃ 8 ድረስ እንዲዘልቅ መደረጉን ጠቁመው በዘርፉ ሥራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ማፍራት የሚያስችል የሙያ ደረጃና ሥርዓተ ትምህርት መዘጋጀቱን አመላክተዋል፡፡
በቀጣይ ከግብርና ማሰልጠኛ ኮሌጆች ሰልጥነው የሚወጡ ዜጎች ዘርፉን ከማዘመንና ምርትና ምርታማነት እንዲረጋገጥ ከሚያደርጉት ሙያዊ ድጋፍ ባለፈ በሙያቸው ኩባንያ እንዲመሰርቱ የሚፈለግ መሆኑን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ለዚህም አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ላለው ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ያሉት የልማት ጣቢያ ባለሙያዎች ናቸው፡፡
ደረጃቸውን ለማሻሻል ያለመው ይህ መርሃ ግብር በዘርፉ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ከማሳደግ ባለፈ ተነሳሽነታቸውን እንዲጨምር የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡
የግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎችን ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችለው መርሃ ግብር በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግም ነው ክቡር ሚኒስትሩ የጠቆሙት።

Read More Âť
News

ከሀገር ውስጥ ባለፈ የዓለም የሥራ ገበያን ለመጠቀም ዜጎችን በክህሎት የማብቃት…

ከሀገር ውስጥ ባለፈ የዓለም የሥራ ገበያን ለመጠቀም ዜጎችን በክህሎት የማብቃት…
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን በውጭ ሀገራት ከሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል አንዱ ነው፡፡
ዜጎች ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ ውጭ ሀገራት እንዲጓዙ ከማድረግ ጀምሮ በመዳረሻ ሀገራት የሚኖራቸው ቆይታም ደህንነታቸው የተረጋገጠ እንዲሆን የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት በሚኒስቴር መ/ቤቱ እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ሚኒስቴር መ/ቤቱ የውል ስምምነት ወደፈፀመባቸው ሀገራት የሚጓዙ ዜጎች በሚሰማሩበት የሥራ መስክ ላይ ብቁ ለመሆን የሚያስችላቸው የክህሎት ሥልጠና በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አማካኝነት እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የክህሎት ስልጠናውን እየሰጡ ከሚገኙ ተቋማት መካከል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም የሆነው የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት አንዱ ነው፡፡
ኢኒስቲትዩቱ ከሃምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሦስት ዙር ከአንድ ሺ ለሚነልጡ ሰልጣኞች የአረብኛ ቋንቋን ጫምሮ በቤት አያያዝ፣ በህፃናትና አዛውንት እንክብካቤና በምግብ ዝግጅት የክህሎት ሥልጠናን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሂደቱን ፈጣንና ቀልጣፈ ለማድረግ እንዲቻልም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስልጠና ብቃት ማረጋገጫ ማዕከል ጋር በመተባበር ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞች የብቃት ምዘና በኢኒስቲትዩቱ ቅጥር ግቢ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በቀጣይ ለ 400 ሰልጣኞች በአራተኛ ዙር ሥልጠናውን ለማስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ከኢኒስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

Read More Âť
News

ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት (World Skills) የሙሉ አባልነት ሰርተፊኬት ተቀበለች!

ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት (World Skills ) የሙሉ አባልነት ሰርተፊኬት ተቀበለች!
የአለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት የኢትዮጵያን 88ተኛ የሙሉ አባልነት የማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ሰጥቷል።
ኢትዮጵያ የአለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት አባል መሆኗ በርካታ ፋይዳዎች ይኖሩታል። ከተለያዩ ሃገራት ጋር የኢንዱስትሪ ትስስር መፍጠር፣ በክህሎት ልማት ከተቀረው የአለም ክፍል ልምድ በመለዋወጥ እንዲሁም በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ልምዶችን በመቅሰም በዘርፉ እየተሠራ ባለው ሥራ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት እና ከተቀረው የአለም የክህሎት ልቀት ጋር እኩል ለመራመድ ሰፊ ምህዳር የሚፈጥር ይሆናል።
አሁን እየተካሄደ በሚገኘው አለም የክህሎት ኦሎምፒክ ላይ ለመሳተፍ እና ከዓለም ጋር እርምጃችንን ለማስተካከል በእጅጉ የረዳን በመሆኑ ትልቅ የስኬት በር ከፋች እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
ለዚህም ስኬት ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ!
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top