Mols.gov.et

mols admin

News

በየአካባቢው የሚገኙ የወጣት ማዕከላት እና የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን…

በየአካባቢው የሚገኙ የወጣት ማዕከላት እና የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ሥራ በማቀናጀት የወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ።
በአዲስ አበባ ከተማ እድሳት የተደረገላቸውን የወጣት ማዕከላት ርክክብና የግብዓት ድጋፍ የተደረገላቸው የአንድ ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ሥራ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።
በርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለፁት፤ የወጣት ማዕከላት እንደሌሎች አንድ ማዕከላት ሥራ ፈላጊዎች የሚመዘገቡባቸው፣ የሥራ ገበያ መረጃ የሚያገኙባቸው እና የወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጡባቸው ለማድረግ ማቀናጀት ይገባል ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በልደታ ክ/ከተማ በመገኘት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሙሉ እድሳት የተደረገለት የወረዳ 9 የወጣት ማዕከልን ቁልፍ ያስረከቡ ሲሆን በአዲሰ ከተማ፣ አራዳ እና በጉለሌ ክፍለ ከተሞች በመንግስት እና በዓለም ባንክ ድጋፍ እድሳት የተደረገላቸው እና ግብዓት የተሟላላቸው አራት የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ሥራ አስጀምረዋል።
የልደታ ወረዳ 09 ወጣት ማዕከልን እና አራቱን የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች በሞዴልነት በመውሰድ ሌሎች የወጣት ማዕከላት እና አንድ ማዕከላትን የማደስ እና በግብዓት የማጠናከር ሥራ እንዲስፋፋም ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አስፋው ለገሰ እና የከተማ አሰተዳደሩ የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

Read More Âť
News

አጋርነት ለውጤት…

አጋርነት ለውጤት…
ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ባይድ ዶው ጋር በቅንጅት መስራት በምንችልባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አካሂደናል፡፡
በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ ላይም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከክህሎት ልማት፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራ እና ከአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ አኳያ ተቀርጸው እየተተገበሩ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎችን በዝርዝር እንደተመለከቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል፡፡
አቶ ሳሙኤል ባይድ ዶው በበኩላቸው እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች መሰታዊ ለውጥ የሚያመጡና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ተሞክሮ የሚሆኑ በመሆኑ ሥራዎቹን ማስፋት እንደሚገባ እና የሪፎርም አጀንዳዎቹን ጨምሮ በጋራ በሚለዩ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተጨባጭ ሥራ ለመስራት ድርጅቱ ዝግጁ እንደሆነ አረጋግጠውልናል፡፡
የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም(UNDP) የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ባይድ ዶው በትኩረት ጉዳዮቻችን ላይ ተጨማሪ አቅም ለመሆንና በጋራ አብሮ ለመሥራት ላሳዩን ቁርጠኝነት እናመሰግናለን በልዋል ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል ፡፡

Read More Âť
News

በክህሎት ልማት ዘርፍ ግንባር ቀደም ለሆኑ ኢንዱስትሪዎች እውቅና ተሰጠ።

በክህሎት ልማት ዘርፍ ግንባር ቀደም ለሆኑ ኢንዱስትሪዎች እውቅና ተሰጠ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ንግድ ማህበራት ምክር ቤት እና ከሌሎችም ባለድርሻ አካላት በትብብር የተዘጋጀው የመጀመሪያው በክህሎት ልማት ላይ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወቱ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች እውቅና ሰጥቷል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ በሬቻ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ የእውቅና ኘሮግራሙ የተዘጋጀው በክህሎት ልማት ላይ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ለማጠናከር እና በዘርፉ አበረታች ስራ የሰሩ ኢንዱስትሪዎች ለበለጠ ስራ እንዲነሳሱ ላበረከቱት አስተዋጽዎ እውቅና ለመስጠት ነው።
መድረኩ የኢንዱስትሪዎች ፍላጎት እና የመንግስት አቅርቦት ላይ ያሉ ጉድለቶችን በጋራ በመለየት ተቀራርቦ ለመስራት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ማህበራት ምክርቤት ኘሬዝዳንት ኢንጅነር መላኩ አዘዘ በበኩላችው፤ በክህሎት ልማት ላይ የግሉ ዘርፍ ጠንካራ ተሳትፎ በዘርፉ ፈጠራን በማበረታታት ዘላቂ የሆነ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል።
በመድረኩ የግሉ ዘርፍ እና መንግስት የተሳተፋበት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን በክህሎት ልማት ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ 24 ኢንዱስትሪዎች የእውቅና ሰርተፍኬት እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

Read More Âť
News

የአይሶ(ISO) 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።

የአይሶ(ISO) 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት፣ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ፀድቆ ተግባራዊ የሚደረገው የጥራት ሥራ አመራር አገልግሎት ISO 9001:2015 በእያንዳንዱ የሥራ ክፍል የሚከናወኑ ተግባራትና አሰራራቸው በቅደም ተከተል የመለየት ሥራ ተከናውኗል።
በዚህም በተቀመጠው የጥራት የደረጃ አግባብ ለመተግበር እና ለማስተግበር ከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት አለ ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነቢሃ መሀመድ በበኩላቸው ተግባራዊ የሚደረገው የጥራት ጀረጃ በሚኒስቴሩ የሚሰጡ አገልግሎቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ የተገልጋይ እርካታ የሚያሳድግ እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው ለዚህም 576 የሚሆኑ የጥራት ደረጃ ሰነዶችን በማዘጋጀት ለትግበራ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በመድረኩ የተገኙት የየዘርፉ ሚኒስትር ዴኤታዎች ስርዓቱ በአግባቡ ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ISO 9001:2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥራ ላይ አስተዋጽዎ ያበረከቱ አመራርና ባለሙያዎች እውቅ ተሰጥቷቸዋል።

Read More Âť
News

ቅንጅት ለዘላቂ ተጠቃሚነት…

ቅንጅት ለዘላቂ ተጠቃሚነት…

የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ወርሀዊ አፈፃፀም እና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ እና የባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡

በውይይቱ የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ቅድሚያ በሰጠው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን፣ የገጠሙ ተግዳሮቶችን እና ተግዳሮቶቹን ለመሻገር የተወሰዱ እርምጃዎችን በዝርዝር መመልከታቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል፡፡

አክለውም በውይይቱ ላይ ዜጎች የመዳረሻ ሀገራትን ፍላጎት ባማከለ መልኩ መሰረታዊ የሙያ ስልጠና አግኝተው ስምሪት እንዲሰጣቸውና አገልግሎት አሰጣጡ በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን መደረጉ እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረው ሥራ ተስፋ ሰጪ ውጤት እንዳመጣና ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተግባብተናል ብለዋል ፡፡

ከአፈፃፀሙ ባለፈ የ2017 በጀት ዓመት የጋራ ዕቅድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ዕቅዱ ከአቅርቦት፣ ከአግልግሎት አሰጣጥ እና ከፍላጎት አኳያ የተለዩ ማነቆዎችን በአግባቡ መፍታት የሚችል መሆኑን ሁሉም ባለድርሻ አካላት አረጋግጦ ወደ ሥራ ለመግባት ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ አቅጣጫ አስቀምጠናል፡፡

ከውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አኳያ በቀጣዩም ዋነኛ የትኩረት ማዕከሉ የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው፡፡ ይህም ዘላቂ እንዲሆን በዘርፉ ህግና ስርዓትን ማስከበር ትኩረት የሚሰጠው ይሆናል ብለዋል፡፡

ክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ ለዘርፉ እየሰጡት ላለው እሴት አካይ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንዲሁም በጋራ ዕቅዳችን መሰረት ርብርብ እያደረጉ ላሉ ባለድርሻ አካላት በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናም አቅርበዋል፡፡!

Read More Âť
News

ፀጋዎቻችንን አልምቶ ከመጠቀም ባለፈ…

ፀጋዎቻችንን አልምቶ ከመጠቀም ባለፈ…
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መሥተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ ላይ በክልሉ ያለውን ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የሚሹ ሥራዎችን መመልከት ተችሏል፡፡
በዚህም የእሴት ሰንሰለትን መሰረት ያደረገው ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅጣጫችን እሴት አካይ ድጋፍና ክትትል እንደሚያስፈልገው እና ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ወደ ህብረተሰቡ ማድረስ እንደሚያስፈልግ የጋራ ሀሳብ ተይዟል።
ከውይይቱ ባለፈ በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዓለም አቀፍ እውቅና ባገኘው የብየዳ ማዕከል በልዩ የክረምት ወራት የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ እና የፈጠራ ሀሳቦች ማሻሻያ መርሃ ግብር እየተሰሩ ያሉ ቴክኖሎጂዎችን በጋራ ተጉብኝተዋል፡፡ በዚህም በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በአግባቡ አልምቶ ከመጠቀም ባለፈ ተኪ ምርቶች ላይ ሀገራዊ አቅም ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ ጥረቶች እና ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል ።

Read More Âť
News

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ጋር ውይይት አካሂደዋል።
ውይይቱ ከውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አኳያ ሁለቱ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ ነው።
በዚህም በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ላይ የተደረገውን ሪፎርም ተከትሎ በዘረጋው የጋራ የአሰራር ስርዓት የተከናወኑ ሥራዎችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችን እና ችግሮቹን ለመሻገር የሚወሰዱ እርምጃዎችን በዝርዝር ተመልክተዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግልጽና የተቀላጠፈ አሰራር ስርዓትን በማስፈን የተጀመሩትን በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥራዎችን ማላቅ በሚያስችል መልኩ የሚዘጋጅበት ሁኔታ ላይም መክረዋል፡፡

Read More Âť
News

በዘርፉ ተግባረዊ እየተደረጉ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ የፌዴራል ተቋማት ሱፐርቪዥን ቡድን አስታወቀ።

በዘርፉ ተግባረዊ እየተደረጉ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ የፌዴራል ተቋማት ሱፐርቪዥን ቡድን አስታወቀ።
በፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስተባባሪነት የፌዴራል ተቋማት ሱፐርቪዥን ቡድን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት እና በአዲስ አበባ በሚገኙ ኮሌጆችና የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ሲያደርግ የነበረውን የመስክ ምልከታ አጠናቋል፡፡
ቡድኑ የመስክ ምልከታውን ማጠናቀቁን ተከትሎ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከተጠሪ ተቋማቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የመውጫ ውይይት አካሂዷል፡፡
በዚህም ተቋማቱ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከማፍራት ባለፈ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በፈጠራ ሥራ እንዲሁም ተኪ ምርቶችን በማምረት በሂደት ራሳቸውን በበጀት እንዲችሉ እያከናወኑ ያለው ሥራ ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ አመላክቷል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ተግባራዊ እያደረገ ያለው የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የሱፐርቪዥን ቡድኑ አስተባባሪና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ ጠቁመዋል።
በዚህም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በሂደት በበጀት ራሳቸውን እንዲችሉ፣ ቴክኖሎጂ ለማልማትና ተኪ ምርቶችን ለማምረት እንዲሁም ፈጠራን ለማበረታታት የጀመሩት ሥራ ጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሥራ ዕድል ለመፍጠር ሚኒስቴሩ እያከናወነ ያለውን ሥራ የሚበረታታ መሆኑንም አመላክተዋል።
የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ጋር በተያያዘ የዜጎችን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅና ህገወጥነትን ለመከላከል በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚሰጠው አገልግሎት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ተደራሽነቱን ለማስፋትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን የቅንጅት ሥራ ለማስፋት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።

Read More Âť
News

የሠራተኛውን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ምርታማነቱን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ ፡፡

የሠራተኛውን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ምርታማነቱን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በአዲስ አበባ የዓለማቀፉ የሠራተኞችን ቀን በሚከበርበት መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በዚህም የዓለም አቀፉን የሠራተኞች ቀን ስናከብር ሠራተኛው መብቱን በተደራጀ መንገድ ለማስከበር ያለፈበትን የትግል ታሪክ ሂደት በመዘከርና ታጋዮቹን በማክበር ብቻ ሳይሆን የአሁኑን የሚመጥን እና የቀጣዩን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ ሥራ ለመስራት ቃላችንን በማደስ መሆን አለበት ብለዋል፡፡
በሀገራችን ከሠራተኛው በየጊዜው የሚነሱ ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ጥናት ላይ ተመስርቶ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በተለየ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሁሉ ተቀራርቦ እየሠራም እንደሆነ በመድረኩ ላይ አንስተዋል፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢንዱስትሪ ሰላምንና የሙያ ጤንነትና ደህንትን ለማረጋገጥ፣ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነቱን ለማሻሻል እና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል አዲስ እሳቤ ቀርጾ ተግባራዊ እያደረገ እንደሆነም አመላክተዋል፡፡
በአሠሪና ሠራተኛ መካከል ያለው ግንኙነት ጤናማ የሚሆነው እና የሠራተኛው መብትና ጥቅም በዘላቂነት የሚከበረው ምርታማነቱ ሲያድግ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም አሠሪው የሠራተኛው ሁለንተናዊ ብቃቱ እንዲያድግ፣ የሙያ ጤንነቱና ደህነቱ እንዲከበር ማድረግ እንዲሁም ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ይኖርበታል ብለዋል፡፡
የሙያ ደህንነትና ጤንነት እንዲሁም የሥራ ሁኔታዎች ቁጥጥር ጋር ተያይዞ የዘርፉ ማነቆ የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት መሆኑን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ችግሩን ለመሻገር በዘርፉ በቂ የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራት የሚያስችል ሥርዓተ ስልጠና ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ ሥራውን በቴክኖሎጂ ለማገዝም ሰፊ ጥረቶች እተደረጉ ነው ብለዋል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ ምርታማነትን ለማሳደግ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣጥ እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ፣ ምርታማነትን እንዲያድግ እና የአሠሪና ሠራተኛው ጥቅም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ ሁሉም በጋራ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ካሣሁን ፎሎ በበኩላቸው፤ የሠራተኞች መሰረታዊ ጥያቄዎች በሂደት ምላሽ እንዲያገኙ ከመንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

Read More Âť
News

የአፍሪካን ኢንዱስትሪያላይዜሽን ለማፋጠን ወጣቶችን በክህሎት ማነጽ እንደሚገባ ተጠቆመ

የአፍሪካን ኢንዱስትሪያላይዜሽን ለማፋጠን ወጣቶችን በክህሎት ማነጽ እንደሚገባ ተጠቆ
ስድስተኛው የአፍሪካ የተግባራዊ ሳይንስ፣ የምህንድስና እና የኢንጂነሪንግ (PASET) አጋርነት ፎረም በኬንያ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የአባል ሀገራቱ የትምህርትና ሥልጠና ሚኒስትሮች፣ አጋር እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል፡፡
በዚህም የአፍሪካን ኢንዱስትሪያላይዜሽን ለማፋጠን የቴክኒክና ሥልጠና ተቋማት የማይተካ ሚና እንዳላቸው እና ወጣቶችን በክህሎት ማነጽ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በመድረኩ ላይ በተወካያቸው በኩል ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢኮኖሚ እድገት እውን በማድረግ ሁሉን አቀፍ እድገት ለማስመዝገብ የአፍሪካን ወጣቶች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በምህንድስና ማነጽ ይገባል።
በአሁጉሪቱ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ለበርካታ የሰው ሃይል የሥራ ዕድል ለመፍጠር እና የሚታሰበውን ኢንዱስትሪያላይዜሽን እውን ለማድረግ የክህሎት ስልጠና የማይተካ ሚና ይጫወታል፡፡
ስለሆነም አፍሪካን ወደ አዲስ የኢንዱስትሪ የዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር ለክህሎት ልማት ልዩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የፎረሙ አባል ሀገራት ከክህሎት ልማት እና ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮሯቸውን አካፍለዋል፡፡
ፎረሙ ኢንትዮጵያን ጨምሮ 12 ሀገራትን (ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጋና፣ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ቤኒን፣ ታንዛኒያ፣ ሶማሊያ እና ቡርኪናፋሶ) በአባልነት ያቀፈ ነው፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top