Mols.gov.et

mols admin

News

ኮሌጁ ለአካባቢው አርሶ አደሮች እና ለተደራጁ ወጣቶች ..

ኮሌጁ ለአካባቢው አርሶ አደሮች እና ለተደራጁ ወጣቶች የተሻሻሉ የእንስሳትና የዕጸዋት ዝርያዎችን እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ
የአላጌ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ማሰልጠኛ ኮሌጅ የተሻሻሉ የእንስሳትና የዕጸዋት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች እና ለተደራጁ ወጣቶች መሰጠቱን አስታወቀ፤
በአላጌ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንተርፕራይዝ ምክትል ዲን የሆኑት ትምህርቱ ሳህሉ (ዶ/ር) እንደገለጹ፤ በትምህርት ማሰልጠኛ ኮሌጁ ውስጥ ከማሰልጠን በተጨማሪ የተለያዩ የምርምርና ጥናቶች እየተካሄዱ ይገኛሉ፡፡
በጥናትና ምርምር ማዕከላቱ የአየር ንብረትን መቋቋም የሚችሉ የአትክልትና የፍራፍሬዎች ችግኞችን የማፍላት ሥራ ተሰርቷል፡፡
150 ለሚደርስ አርሶ አደሮች ተገቢ የሆነ ሥልጠና እንዲያገኙ በማድረግም የተሻሻሉ የኮርማ፣ የፍየልና የጊደር ዝርያዎችን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
ከ3 ቀበሌ ለተውጣጡ 30 ወጣቶች የኦርጋኒክ ኮምፖስት ማዳበሪያ አዘገጃጀት ሥልጠና መስጠቱንም ነው የኮሌጁ ም/ል ዲን ያመላከቱት፡
በዚህ ዓመት በ6 ቀበሌ ገበሬ ማህበራት እና በ3 የወረዳ ከተሞች አስከ ሰባት መቶ አምሳ ሽህ የሚደርሱ የተለያየ ዝርያ ያላቸው የሙዝ፣ የቡና፣ የፓፓያ፣ የሞሪንጋ እና ሌሎች ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን በማዘጋጀት ወደ ህብረተሰበቡ ለማድረስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
ዶክተር ትምህርቱ አክለውም የኮሌጁንና የአካባቢውን ማህበረሰብ በጋራ የሚያስተባብር ልዩ ኮሚቴ መቋቋሙን ጠቁመው ሃምሌ 18 ቀን 2016 ዓ.ም የኮሌጁንና የአካባቢውን ማበረሰብ የሚያሳትፍ የችግኝ ተካላ ፕሮግራም ይካሄዳል ብለዋል ፡፡

Read More »
News

“የጥናትና ምርምር ሥራዎች ፋይዳ የሚኖራቸው ወደ ተግባር መሸጋገር ሲችሉ ነው፡፡”

“የጥናትና ምርምር ሥራዎች ፋይዳ የሚኖራቸው ወደ ተግባር መሸጋገር ሲችሉ ነው፡፡”
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩና በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት የተጠኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የሚኒስቴሩ ካውንስል አባላት እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለፁት፤ የተጠኑ ጥኖቶች እቅዶቻችን ላይ እሴት መጨመር በሚያስችል መልኩ መተግበር አለባቸው። ጥናቶች ፋይዳ የሚኖራቸው ወደ ተግባር መሸጋገር ሲችሉ ነው ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በበኩላቸው ጥናቶቹ እንደ ሀገር እጅግ ወሳኝ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰው ወደ ተግባር መሸጋገር እንዲችሉ ወደ ስርዓት ትምህርት እየቀየሩ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የጥናትና ምርም ስራዎቹ በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች (Technology Mapping on Prioritized Government Development Sectors, Study on TV related Indigenous Knowledge and Skills in Ethiopia and Implementation of Zoning and Differentiation Initiatives: Brief Assessment) ያተኮሩ ናቸው፡፡

Read More »
News

‹‹የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ችግር ፈቺ እና መፍትሄ አመንጪ በመሆኑ ለሀገር ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያለው ዘርፍ ነው››

‹‹የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ችግር ፈቺ እና መፍትሄ አመንጪ በመሆኑ ለሀገር ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያለው ዘርፍ ነው››
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ከ2100 ሰልጣኞችን በመጀመሪያ(ደረጃ 6) እና በሁለተኛ (ደረጃ 7) ዲግሪ ዛሬ አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስክ ችግር ፈቺ እና መፍትሄ አመንጪ በመሆኑ ለሀገር ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያለው ዘርፍ ነው፡፡
ዘርፉ እንደ ሀገር ያለምናቸውን ግቦች ከማሳካት አንፃር የሚያበረክተውን ጉልህ አስተዋፅኦ ከግምት በማስገባትም የፖሊሲ ማዕቀፍ በመቅረፅ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ ሰጪ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሥርዓትን ችግር ፈቺና መፍትሔ አመንጪ እንዲሆን ለማስቻል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አዳዲስ የለውጥ እሳቤዎችን ቀርፆ ወደ ሥራ መግባቱን ጠቁመዋል፡፡
ይህም የሥልጠና ጥራትን፣ ውጤታማነትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ቁልፍ ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑንም አንስተዋል።
በዘርፉ የሚሰጠውን ስልጠና ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ በማሳደግ መላው ዜጎች በተመሳሳይ የክህሎት ልማት ራሳቸውን እንዲያበቁ በሚያስችል መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
ሥልጠና ለቀጣዩ የህይወት ምዕራፍ ጉልበትን፣ ዕውቀትን እና ጥበብን የሚያጎናፅፍ ትልቅ ዕድል መሆኑን ያመላከቱት ክብርት ሚኒስትር ተመራቂዎች በደረሱበት ደረጃ ብቻ ረክተውና ተወስነው ሳይቀሩ ለራሳቸውና ለሀገራቸው ትርጉም ያለው ሥራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

Read More »
News

አነስተኛ ወጪ፣ ትልቅ ተጽዕኖ፤ ለሚሊዮኖች ተስፋ የሆነው የሰመር ካምፕ ውጤት…

አነስተኛ ወጪ፣ ትልቅ ተጽዕኖ፤ ለሚሊዮኖች ተስፋ የሆነው የሰመር ካምፕ ውጤት…
በአሁን ወቅት ቤት መስራት ለበርካቶች እጅግ ከባድ እየሆነ መጥቷል፡፡ የቤት ግንባታን ፈታኝ ካደረጉት ጉዳዮች መካከልም ከመሬት ዋጋ ባሻገር የመሥሪያ ግብዓት ዋጋ መናር ተጠቃሽ ምክንያት ነው።
ቤት ከሚሰራባቸው ግብዓቶች መካከል ደግሞ አንዱ ብሎኬት ነው፡፡ የብሎኬት ዋጋ በቤት አቅርቦት እና ዋጋ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚያመጣም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነገራል፡፡ ለብሎኬት ዋጋ እና ምርት ደግሞ የሲሚንቶ አቅርቦት እና ዋጋ ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ የብሎኬትን ዋጋ ለማረጋጋት ሲሚንቶን የሚተካ አማራጭ ማሰብ ሌላኛው መፍትሄ ነው፡፡
ይህንን የተገነዘቡት ግርማ እና ጓደኞቹ ለዚህ ችግር መፍትሄ ያሉትን ቴክኖሎጂና በቴክኖሎጂውም የሚሰራውን ተሰካኪ(interlocking) ብሎኬት ይዘው ብቅ ብለዋል፡፡
ማሽኑን ለመስራት የተነሳሱት ከዚህ ቀደም ለዚህ አገልግሎት ከቻይና የሚገባው ማሽን በመጠኑ ትልቅ፣ በዋጋው ውድ እንዲሁም ጥገናውም አዳጋች በመሆኑ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
በአንጻሩ አሁን የሰሩት ማሽን የትም ቦታ ተነቃቅሎ በቀላሉ ማንቀሳቀስ የሚቻልና በቀላል ወጪ የሚጠገን እንዲሁም በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ መቅረብ የሚችል ማሽን መሆኑን ይገልጻሉ፡፡
ይህንን ማሽን ተጠቅመው የሚያመርቱት ብሎኬትም የአገልግሎት እድሜው ከመደበኛው ብሎኬት እጅግ ረዥም ዓመት የሚያገለገል መሆኑ መረጋገጡንም ያስረዳሉ፡፡
በዚህም በተለይ የገጠር ቤቶችን ለመቀየር እና ቤት የመስራት አቅሙ የሌላቸው ዜጎች እጅግ ባነሰ ወጪ ቤት እንዲገነቡ ያደርጋል ይላሉ፡፡
የማምረቻ ማሽኑን እና ብሎኬት በስፋት አምርቶ (mass production) ለገበያ የማቅረብ ፍላጎት ያላቸው ግርማ እና ጓደኞቹ ህልማቸውን ለማሳካት በአሁን ወቅት ሙሉ ሥራዉን አጠናቀው የሙከራ ደረጃ ላይ አድርሰውታል፡፡
ይህ ማሽን በኤሌክትሪክ ኃይልና በማንዋል የሚሠራ ሲሆን የማምረት አቅሙንም በማኑዋል በቀን እስከ 5 መቶ ተሰካኪ ብሎኬት፤ በኤሌክትሪክ ደግሞ እስከ አንድ ሺህ ብለኬት ማምረት እንደሚያስችል ነው የተነገረው፡፡
ግርማ እና ጓደኞቹ ይዘው የመጡት ቴክኖሎጂ በሀገራችን ለሚሊዮኖች ተስፋ የሆነ ከመሆኑም ባሻገር እንደ ሀገር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በተፈጥሮ ሀብት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት በእጅጉ በመቀነስ ጤናማ የኑሮ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይታመናል፡፡
ከቤንሻጉል ጉሙዝ ክልል፣ ከደብረብርሃን እና ከወላይታ ሶዶ መጥተው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት ጋር ባዘጋጁቱ የክረምት ልዩ ቆይታ(summer camp) የተገናኙት እነዚህ ወጣቶች ባላቸው የተቀራረበ ክህሎት እና ማሳካት በሚፈልጉት ያጋራ ህልም በአንድ ተደራጅተው ወደ ትልቅ ኢንተርፕራይዝ ለመሸጋገር እየተጉ ይገኛሉ፡፡

Read More »
News

በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ጥራትና አግባብነትን በማሻሻል ለሥራ ገበያው..

ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ጥራትና አግባብነትን በማሻሻል ለሥራ ገበያው የሰው ሃየይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ፋይዳው የላቀ እንደሆነ ተጠቆመ።
በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ተግባራዊ የሚደረገው EASE (Ethiopia Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት የትግበራ ምዕራፉን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ።
በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ከሚል እና በዓለም ባንክ ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ ሁማ አሊ ዋሂድን ጨምሮ የሚኒስቴሩና የድርጅቱ የሥራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ የፕሮጀክቱ የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት በዝርዝር ተገምግሞ
የትግበራው ምዕራፍ ላይ አቅጣጫ ተሰጥቶበታል፡፡
በውይይቱ በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ጥራትና አግባብነትን በማሻሻል ለሥራ ገበያው የሰው ሃይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም መንግስት ለሴቶችና ወጣቶች ምቹና ዘላቂ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የጀመረውን ጥረት ፕሮጀክቱ በእጅጉ የሚያግዝ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡
EASE ፕሮጀክት ከዓለም ባንክ በተገኘ 200 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በሚሆን በጀት ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን ለትግበራው ውጤታማነት በየደረጃው ያለ የዘርፉ አመራር ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባውም ተጠቁሟል፡፡

Read More »
News

ሚኒስቴሩ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለው…

ሚኒስቴሩ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን ውይይት አካሄደ
በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሰን ጨምሮ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በዚህም ሁለቱ ተቋማት በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
ይህ ትብብር ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ብቁና በቂ ባለሙያዎችን በማቅረብ፣ የሙያ ደህንነትና ጤንነትን በማረጋገጥ እንዲሁም ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት በመፍጠርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በዘርፉ የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችን ማሳካት የሚያስችል እንደሆነ በውይይቱ ላይ ተመላክቷል።
በተለይ በሚኒስቴሩ በልጽጎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የኢትየጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓትን ከኮርፖሬሽኑ የሥራ ባህሪ ጋር አጣጥሞ መጠቀም እንደሚያስፈልም የተጠቆመ ሲሆን ተቋማቱ በትትብብር የሚሠሩ ዝርዝር ሥራዎችን የለየ የጋራ ዕቅድ አቅዶ ወደ ሥራ ለመግባት ተስማምተዋል።

Read More »
News

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋማት የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች…

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋማት የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመግም የውይይት መድረክ ተካሄደ ።
የሪፎርም ቡድኑ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ባካሄዱት ውይይት በሚኒስቴር መ/ቤቱና በተጠሪ ተቋማት ከአሰራርና አደረጃጀት አንፃር ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ነባራዊ ትንተና መሰራቱ ተገልጿል ።
በሥራ ላይ ያሉና መሻሻል የሚገባቸው ፖሊሲዎችን ፣ አዋጆችን ደንብና መመሪያዎችን የመለየት ሥራ መሰራቱም በመድረኩ ተጠቁሟል ።
ምቹ የሥራ ሁኔታን ከመፍጠር አንፃር የህፃናት ማቆያ ፣ የካፍቴሪያ፣የሸማቾች ህብረት ሥራና መሰል አገልግሎቶችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም በመድረኩ ተመልክቷል ።
አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ የማድረግ ሥራ ከሁሉም ቅድሚያ እንደተሰጠው የተገለፀ ሲሆን የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የISO 9001፡ 2015 የጥራት ደረጃን የመተግበር ሒደት በሚኒስቴር መ/ቤቱና ተጠሪ ተቋማት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተብራርቷል ።

Read More »
News

በዓለም የሥራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ ለመሆንና ገበያ ውስጥ ለመቆየት ጊዜውን የዋጀ የሕግ ማዕቀፍ ወሳኝ ነው፡፡

በዓለም የሥራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ ለመሆንና ገበያ ውስጥ ለመቆየት ጊዜውን የዋጀ የሕግ ማዕቀፍ ወሳኝ ነው፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አዋጅን ለማሻሻል የሚያስችል የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት መድረክ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚልና የአሠሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል አስፈፃሚ እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስርዓቱን ለማሻሻልና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
በዚህም የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ባረጋገጥ መልኩ እንዲከናወን የተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት አስገኝቷል ብለዋል፡፡
በዓለም የሥራ ገበያ ላይ መወዳደር ብቻ ሳይሆን ገበያ ውስጥ መቆየት ወሳኝ በመሆኑ ተለዋዋጭ የሆነውን ዓለማዊ ሁኔታ ባገናዘበና በሥራ ሂደት የታዩ ክፍተቶችን በዘላቂነት በማረም በዘርፉ ማነቆ የሆኑ የአሰራርና የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻል በማስፈለጉ መድረኩ የተዘጋጀ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
አዋጁን ለማሻሻል በርካታ መነሻ ምክንያቶች እንዳሉት ያመላከቱት ክብርት ሚኒስትር በዘርፉ ተግባራዊ ከተደረጉ የእሳቤ ለውጦች ባሻገር የዜጎችን መብት፣ ደህንነትንና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፤ ብልሹ አሰራሮችን መከላከል እንዲሁም በዘርፉ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ማቃለል ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑም ጠቁመዋል፡፡

Read More »
News

በሚኒስቴሩ የለሙ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

በሚኒስቴሩ የለሙ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የለሙ የቀጠሮ ማስያዣ እና ቅሬታ እና አስተያየት ማቅረቢያ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሚኒስቴሩ አመራርና ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡
ሚኒስቴሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ እና በተቋሙ የሚቀርቡ አቤቱታ እና ቅሬታዎችን መቀበል እና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ የቀጠሮ ማስያዣ(appointment system) እና አስተያየት እና ቅሬታ መቀበያ(public feedback system) በአግባቡ እንዲጠቀሙ ታሳቢ ተደርጎ መድረኩን መዘጋጀቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኃ/እየሱስ ደምሴ ገልጸዋል፡፡
ሀገራት አገልግሎታቸውን ለማዘመን ወደ ዲጃታል ዓለም እየገቡ መሆኑ የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው ሚኒስቴሩም ዘመኑና ጊዜውን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉትን ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ መተግበረያዎችን በማልማት ወደ ሥራ እያስገባ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የተቋሙ ሠራተኞች መረጃ መለዋወጥ የሚያስችላቸውን አፕሊኬሽን( MOLS Family chat application) እና የተቋሙ ሰራተኞች የሀሳብ ባንክ(Idea bank) ሲስተሞች አጠቃቀም አስመልክቶ ገለጻ ተደርጓል፡፡
ባለጉዳዮች ወይም ተገልጋዮች ወደ ሚኒስቴሩ ለመምጣት ቢፈልጉ አስቀድመው ቀጠሮ ለማስያዝ appointment.mols.gov.et እና አስተያየት እና ቅሬታ ለማቅረብ ደግሞ pfs.mols.gov.et በመግባት መስተናገድ እና አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

Read More »
News

“ትኩረታችን ምርትን ብቻ ሣይሆን ምርታማነትን ማሳደግ ነው።”

“ትኩረታችን ምርትን ብቻ ሣይሆን ምርታማነትን ማሳደግ ነው።”
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አመራርና ሠራተኞች በሀገራዊ የዘርፎች አፈፃፀም እና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሄዱ።
በመድረኩ የማክሮ ኢኮኖሚው ሀገራዊ የዘርፎች አፈፃፀምና የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት ዓመት አቅጣጫዎች ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት፣ መድረኩ ሁሉም አመራርና ሠራተኛ በማክሮ ኢኮኖሚው ሀገራዊ የዘርፎች አፈፃፀምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተገቢውን ግንዛቤ ይዞ የድርሻውን መወጣት እንዲችል ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው፡፡
አፈፃፀሙ በአስተቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሆነን መስራትና ውጤታ ማምጣት እንደምንችል ያሳየ ነው፡፡
ይህም በቀጣይ ትጋትና ብርታት መለያችን ሆኖ ከቀጠለ የታሰበውን ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ማድረግ እንደምንችል የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር የተደረገው ጥረትም ተስፋ ሰጪ እንደሆነም ነው ክብርት ሚኒስትር ያመላከቱት፡፡
እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በኢንዱስትሪ ሰላም ዙሪያ የምንሰራተው ሥራ እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ እንደሆነ ያመላከቱት ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ትኩረታችን ምርትን ብቻ ሣይሆን ምርታማነትን ማሳደግና የተሟላ ኢኮኖሚያዊ ነፃነትን ማግኘት ነው። ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ለመወጣት ርብርብ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top