Mols.gov.et

bini

News

ለሥራ ወደ ውጪ የሚሄዱ ዜጎች የሚስተናገዱት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ብቻ ነው፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ለሥራ ወደ ውጪ የሚሄዱ ዜጎች የሚስተናገዱት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ብቻ ነው፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
ለሥራ ወደ ውጪ የሚሄዱ ዜጎች የሚስተናገዱት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ብቻ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ፡፡
ክብርት ሚኒስትር ይህን ያስታወቁት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በነበራቸው ውይይት ላይ ነው፡፡
ሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን በውይይቱ ላይ አንስተዋል፡፡
የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ስርዓቱ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ አንስቶ በስርዓቱ ላይ በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ፈፃሚዎች እንዲሁም ተጠቃሚዎች ግልጽነት እንዲኖራቸው እየተደረገ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መንግስት ከመንግስት፣ መንግስት ከኩባንያ እና ኩባንያ ከኩባንያ ጋር በሚያደርጉት ስምምነት ሊተገበር እንደሚችል ያነሱት ክብርት ሚኒስትር አልፎ አልፎ በግል ጥረት የሚገኙ የሥራ ዕድሎችንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህጋዊ በሆነ መንገድ ሥምሪት እንዲያገኙ ያደርጋል ብለዋል፡፡
ሆኖም በየትኛውም አማራጭ ቢሆን ለሥራ ወደ ውጪ የሚሄዱ ዜጎች የሚስተናገዱት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ብቻ እንደሆነም በአንክሮት አንስተዋል፡፡
የሁለትዮሽ ስምምነት ከተደረሰባቸው ሀገራት ውጪ ዜጎችን ለሥራ እንልካለን የሚሉ አጭበርባሪዎች መኖራቸውን ያነሱት ክብርት ሚኒስትር ህብረተሰቡ እራሱን ከእነዚህ አካላት እንዲጠብቅ አሳስበዋል፡፡

Read More Âť
News

በልምድ የተገኘ ሙያን በምዘና በማረጋገጥ እውቅና መስጠት ስርዓቱ ይበልጥ አካታች እንዲሆን የሚያስችል ነው፡፡ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ

በልምድ የተገኘ ሙያን በምዘና በማረጋገጥ እውቅና መስጠት ስርዓቱ ይበልጥ አካታች እንዲሆን የሚያስችል ነው፡፡
ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
በልምድ የተገኘ ሙያን በምዘና በማረጋገጥ እውቅና መስጠት የዜጎችን ተወዳዳሪነትና ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ስርዓቱ አካታች እንዲሆን የሚያስችል መሆኑ ተጠቆመ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ አንደገለጹት በየዓመቱ ከግማሽ ሚሊን በላይ ዜጎች በመደበኛ ስልጠና ተደራሽ ይሆናሉ፡፡
በገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናም ከሦስት ሚሊየን በላይ ዜጎች የተለያዩ ስልጠናዎችን በመውሰድ የሥራ ገበያውን ይቀላቀላሉ፡፡
በአንፃሩ በርካታ ዜጎች ከመደበኛ ስልጠና ውጪ ባገኙት ሙያ የሥራ ገበያ ውስጥ ገብተው ይሰራሉ፣ ኢኮኖሚውንም በእጅጉ ይደግፋሉ፡፡
ነገር ግን በዚህ መልክ የሚገኝ እውቀትና ክህሎትን የሚያስተናግድ ስርዓት እስከ ቅርብ ጊዜ ስላልነበረን በልምድ የሙያ ባለቤት የሆኑ ዜጎች ተወዳዳሪነታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን በተገቢው ልክ ማሳደግ አይችሉን ነበር ብለዋል፡፡
ይህን ከግምት በማስገባትና የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ ሚኒስቴሩ በልምድ የተገኘ ሙያን በምዘና በማረጋገጥ እውቅና መስጠት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋቱን አመላክተዋል፡፡
በርካታ ዜጎች በልምድ ያገኙትን ሙያ በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች በሥራ ላይ እንዳሉ ያመላከቱት ዶ/ር ተሻለ የኮንስትራክሽን፣ የቱሪዝምና የሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪውን በማሳያነት አንስተዋል፡፡
የተዘረጋው ስርዓት ይህን የሰው ሃይል ብቃቱን፣ ተወዳዳሪነቱ እና ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ ወሳኝ ሚናም እንዳለው ጠቁመዋል፡፡
የሥራ ጥራትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን የሰው ሃይሉን ምርታማነት ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛም እንደሆነ ነው ዶ/ር ተሻለ ያመላከቱት፡፡
የተሻሻለ ሀገራዊ የሠራተኛ ፕሮፋይል እንዲኖረን፣ ማህበራዊ ትስስርን ከማጠናከር፣ የዕድሜ ልክ ትምህርትን ከማበረታታት እንዲሁም በትምህርትና ስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪው መካከል ጠንካራ ትብብር እንዲፈጠር ከማድረግ አኳያ የተዘረጋው ስርዓት ሚናው የላቀ እንደሆነም አመላክተዋል፡፡
ለሥርዓቱ ውጤታማነትም የዘርፉ ተዋንያኖች በሙሉ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉም ሚኒስትር ዴኤታው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

Read More Âť
News

በፍጥነት ሊያሻግረን የሚችለው በአስተሳሰብ ላይ አይነተኛ ለውጥ ማምጣት ስንችል ነው፡፡ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ

በፍጥነት ሊያሻግረን የሚችለው በአስተሳሰብ ላይ አይነተኛ ለውጥ ማምጣት ስንችል ነው፡፡
የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚኒስቴሩ የሪፎርም አጀንዳዎች ዙሪያ ሲያካሂድ የነበረውን ውይይት አጠናቋል፡፡
በማጠቃለያ መድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ እንደገለጹት፣ በሚኒስቴሩ ተቀርፀው ተግባራዊ እየሆኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ ነው፡፡
በዘርፉ በአዲስ ይዘትና አቀራረብ በኢንተርፕሪነርሺፕ ላይ እየተሰጡ ያሉ ስልጠናዎች በዘርፉ እየመጣ ላለው ውጤት ሚናቸው የላቀ ነው፡፡
የአመራሩና የሠራተኛውን አስተሳሰብ በመቀየር ብቻ የውስጥ ገቢያቸው በብዙ እጥፍ ያሳደጉ ተቋማት መኖራቸው ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
እንደ ሀገር በፍጥነት ሊያሻግረን የሚችለው በአስተሳሰብ ላይ አይነተኛ ለውጥ ማምጣት ስን ችል ነው ያሉት የተከበሩ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው ሚኒስቴሩ እንደ ሀገር ያሉንን የልማት ፀጋዎች አሟጦ ለመጠቀም አስተሳሰብ ላይ የሚሠራው ሥራ ወሳኝ መሆኑን በአንክሮ ገልፀዋል ፡፡
ለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ከሆኑ ተቁማት አንዱ በሆነው አንተርፕር ነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት አማካኝነት የተጀመረው ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው መድረኩ የድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሥራቸውን በእጅጉ የሚያግዝ እንደሆነ ጠቁመው የተጀመሩ ውጤታማ ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው መቀ ጠል አለባቸው ብለዋል፡፡

Read More Âť
News

ሚኒስቴሩ ካጉል(kagool) ከተሰኘ ዓለም አቀፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል አቅራቢ ድርጅት ጋር በትብብር ለመሥራት የሚያስችለውን ውይይት አካሄደ፡፡

ሚኒስቴሩ ካጉል(kagool) ከተሰኘ ዓለም አቀፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል አቅራቢ ድርጅት ጋር በትብብር ለመሥራት የሚያስችለውን ውይይት አካሄደ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ከድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በውይይቱ ካጉል ዓለም አቀፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል አቅራቢ ድርጅት በኢትዮጵያ በአይሲቲ ዘርፍ ባለሙያዎችን አሰልጥኖ ለዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ እንደሚያቀርብ ተጠቁሟል፡፡
በዚህም የኮደርስ ስልጠና የወሰዱትን ጨምሮ በዘርፉ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ዜጎች ድርጅቱ የሚሰጠውን ስልጠና ካጠናቀቁ በኋላ በስመ ጥር የቴክኖሎጂ ተቋማት በአውት ሶርሲንግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገኘው ሰፊ የወጣት ሀይል፣ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተጀመረው የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና፣ በርካታ የስልጠና ተቋማት መኖር እና በቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኢትዮጵያ እየሰራቻቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ኩባንያው በኢትዮጵያ በዘርፉ እንዲሰማራ ሳቢ ምክንያቶች እንደሆነም ተመላክቷል፡፡

Read More Âť
News

ሚኒስቴሩ በቴክኖሎጂ ታግዞ ፈጠራን፣ ጥራትንና ፍጥነት አስተሳስሮ እየሠራ ያለበት መንገድ የሚደነቅ ነው፡፡ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ

ሚኒስቴሩ በቴክኖሎጂ ታግዞ ፈጠራን፣ ጥራትንና ፍጥነት አስተሳስሮ እየሠራ ያለበት መንገድ የሚደነቅ ነው፡፡
የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ የተመራ የምክር ቤቱ ጉዳዮች አማካሪና አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የሠው ሀብት ልማት ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና በተጠሪ ተቋማቱ የሥራ ምልከታ አድርገዋል፡፡
በምልከታው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና በተጠሪ ተቋማቱ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ሥራዎች ታይተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ባለፉት ሦስት ዓመታት ሚኒስቴሩ ያከናወናቸውን የሪፎርም ሥራዎች አስመልክተው ለምክር ቤቱ ኮሚቴ አባላት ማብራርያ እና ገለጻ አድርገዋል፡፡
የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ሚኒስቴሩ እጅግ ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተበታተነውን የሰው ሀይልና ሀብት አደራጅቶ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን ጠቁመው ለዚህም በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጠራን፣ ጥራትንና ፍጥነትን አስተሳስሮ እየሠራ ያለው ሥራ ውጤታማ አድርጎታል ብለዋል፡፡
በጉብኝቱ የታዩት ሥራዎች ብልጽግናን እውን ለማድረግ የተቀመጡ የመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎች እየተተገበሩ ስለመሆናቸው ማሳያ እንደሆነ የጠቆሙት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ምክር ቤቱ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ድጋፍ በሚያስፈልገው ጉዳች ላይ ለማገዝ ግንዛቤ እንዲኖረው ያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

Read More Âť
News

ከንብ ትጋት የተቀሰመ ጣፋጭ ስኬት

ከንብ ትጋት የተቀሰመ ጣፋጭ ስኬት
ነዋሪነቱ በድሬዳዋ ከተማ የሆነው አቶ አብዱልቃድር ሁሴን እብራሂም ከዓመታት በፊት ከተማረው ኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርት ጋር የተያያዘ ሥራ ላይ ነበር የተሰማራው፡፡
የሥራው ባህሪ ሆኖ ረጅም ሰዓት ተቀምጦ መቆየቱ የሚያመጣውን የሰውነት ክብደት እና ተያያዥ የጤና ችግሮች ለመከላከል በቀን የተወሰነ ሰዓት ጎንበስ ቀና ብሎ ሊሠራው የሚችለውን ሥራ ማሰብ ጀመረ፡፡
በቤተሰቦቹ ግቢ ውስጥ አትክልትና ፍራፍሬ ማልማት በሃሳቡ ከመጡ ሥራ አይነቶች መካከልም ቀዳሚው ነበር፡፡ ሥራውን እንደ አካል ብቃት እንቅስቃሴም ጭምር በመውሰድ ቲማቲም፣ ጎመን ቃሪያ የመሳሰሉ የጓሮ አትክልቶችንና እንደ ብርቱካንና ሎሚ የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን ማልማት ጀመረ፡፡
እንደ ቀላል የጀመረው ሥራ እያደገና እየተስፋፋ ሲሄድ ከቤተሰብ ፍጆታ አልፎ የገቢ ምንጭም መሆን ከመቻሉም በላይ አቶ አብዱልቃድር ለግብርና ሥራዎች ምን ያህል ፍቅርና ፍላጎት እንዳለውም ጭምር ያስተዋለበት አጋጣሚ ነበር፡፡
የመኖሪያ ግቢው በአትክልትና ፍራፍሬ ሙሉ በሙሉ ሲሸፈን ደግሞ ከግብርና ባለሙያዎች ባገኘው ምክር አንድ የንብ ቀፎ ገዝቶ ወደ ንብ ማነብ ሥራ ገባ፡፡
አቶ አብዱልቃድር ለንብ ማነብ ሥራው አዲስ በመሆኑ ሥራውን በጀመረበት ወቅት በጣም ተቸግሮ እንደነበርና የሚጠበቀውን ያህል የማር ምርት እንዳላገኘም ይናገራል፡፡ ይህን ክፍተት ለመሙላት በንብ እርባታ ላይ የተፃፉ ፅሁፎችንና የሬድዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራሞችን መከታተል እንዲሁም ከባለሙያዎች ጋር መመካከር የዕለት ተዕለት ተግባሩ ሆነ፡፡
በሥራው ላይ ያለው ዕውቀት እየጨመረ ሲመጣም በቅድሚያ አስር ባህላዊ ቀጥሎም ወደ ዘመናዊ የሚያሻግሩ 15 ቀፎዎችን እና 2 ዘመናዊ ቀፎዎችን ገዝቶ የንብ ማነቡን ሥራ በሰፊው ተያያዘው፡፡
በጊዜ ሂደትም ዘመናዊ ቀፎዎችን መጠቀም ምርታማነትም ሆነ ጥራት ለመጨመር የሚያስችል መሆኑን በመረዳቱ በ50 ዘመናዊ እና በ27 የሽግግር (የባህላዊና ዘመናዊ ቀፎ ባህሪን አጣምረው የያዙ) ቀፎዎችን በመጠቀም በዓመት አስከ 100ኪ.ግ የሚደርስ ማር ማምረት ቻለ፡፡
‹‹የሙያ ፍቅርና የቢዝነስ ክህሎት›› አንድ ላይ ሲጣመሩ ውጤታማ ያደርጋሉ የሚለው አቶ አብዱልቃድር ለንብ ማነብ ሥራ ያደረበትን ጥልቅ ፍቅር በስኬታማ ቢዝነስ ለመደገፍ የሚስችሉትን አማራጮች ዘወትር ከማማተር ወደኋላ ብሎ አያውቅም፡፡
ባካሄደው ጥልቅ ምልከታም ምንም እንኳን ድሬዳዋ ሞቃታማ የአየር ፀባይና በአካባቢው የሚበቅሉ እፅዋት ለንብ ማነብ ሥራ ምቹ ቢሆንም በአካባቢው በቂ የንብ መንጋ የማግኘት ችግር መኖሩን ተገነዘበ፡፡
ንብ ማባዛትና ማከፋፈል አስመልክቶ በግል ጥረቱ ባገኘው ዕውቀት መነሻነት የንብ መንጋዎች እያባዛ ለግብርና ቢሮዎች፣ በመስኩ የሥራ ዕድል ለሚፈጠርላቸው ወጣቶችና የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች ከ7ሺ እስከ 20ሺ ብር በሚያወጣ ዋጋ ከአንድ መቶ በላይ መንጋዎችን መሸጥ እንደቻለ ይናገራል፡፡
አቶ አብዱልቃድር በአሁኑ ጊዜ ከማር ምርትና ከንብ መንጋ ሽያጭ በተጨማሪ የማር እንጀራ በመጋገር ለገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ በሥራው ላይ ለመሰማራት ለሚፈልጉ የአካባቢው ወጣቶች ስልጠናም ይሰጣል፡፡
ከንብ ማነብ ጋር በተያያዘ ያለውን ዕውቀትና ክህሎት ለማዳበር በየዕለቱ ቢያንስ ለአንድ ሰዓት ዘርፉን አስመልክተው የተዘጋጁ ፅሁፎችን እንደሚያነብ ይናገራል፡፡ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአውሮፓ ፈንድ የሚደገፍና በዘርፉ የሚሰጥ ዓለም አቀፍ ስልጠናን በኦንላይን ተከታትሎ የምስክር ወረቀት ባለቤት መሆን የቻለ ሲሆን በ2025 በዴንማርክ፣ ኮፐንሃገን በሚካሄደው ‹‹ዓለም አቀፍ የንብ ማህበረሰብ ጉባኤ›› ላይ ተሳታፊ ለመሆንም ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
አማርኛ፣ ኦሮምኛ ሶማልኛና እንግሊዘኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፎ የሚናገረው አቶ አብዱልቃድር ‹‹የምስራቅ አፍሪካ የንብ ማህበረሰብ›› ለመፍጠር የዋትሳፕ ፕላትፎርምን በመጠቀም በሶማሊያ፣ በኬኒያ፣ በኢትዮጵያና ታንዛኒያ የሚገኙ 350 በመስኩ የተሰማሩ ሶማልኛ ቋንቋ ተናጋሪዎችን በግሉ ማሰባሰብ እንደቻለ ይናገራል፡፡ በአማራና ትግራይ ክልል ከተቋቋሙ መሰል ፎረሞች ጋር የፈጠረው ግንኙነትም አዳዲስ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም በር ከፍቶለታል፡፡
አቶ አብዱልቃድር የማር ምርት በምስራቅ አፍሪካ ገበያ ላይ ከፍተኛ ተፈላጊነት ያለው መሆኑን በመረዳቱም በሥፋት ለማምረት የሚያስችል የመሬት ጥያቄ ለድሬዳዋ አስተዳደር አቅርቦ ምላሽ እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ የመሬት ጥያቄው ምላሽ ሲገኝም በዓመት 40ሺ ኪሎ ግራም ማር አምርቶ ወደ ውጭ የመላክ ዕቅድን ይዟል፡፡
ከራሱ አልፎ የአካባቢውን ማህበረሰብም ጭምር ተጠቃሚ ለማድረግ ለአርሶ አደሮች ተገቢውን ሥልጠና በመስጠት፣ ጥራት ያለውን የንብ መንጋ በማቅረብና የምርት ሂደታቸውን በመቆጣጠር አብሮ ለመስራት የሚያስችል ዕቅድ መንደፉንም ይናገራል ፡፡

Read More Âť
News

የአሠሪና ሠራተኛ ማህበራት- ለምርታማነት

የአሠሪና ሠራተኛ ማህበራት- ለምርታማነት
ሠራተኞች የሥራ ሁኔታቸውን ለማሻሻል፣ መብትና ጥቅማቸዉን ለማስከበርና የኢንዱስትሪ ሠላምን ለማረጋገጥ በማህበር የመደራጀት፣ የመመካከርና የመደራደር መብት እንዳላቸው በአለም ሥራ ድርጅት ድንጋጌ 87/1948 እና 98/1949 በግልፅ ሰፍሯል፡፡
የሀገራችን የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 113/1 ሠራተኞችና አሠሪዎች እንደአግባቡ የሠራተኞች ወይም የአሠሪዎች ማህበር ለማቋቋምና ለማደራጀት፣ የማህበር አባል ለመሆን እና በማህበር ለመሳተፍ መብት እንዳላቸው ይገልፃል፡፡
በሌላ በኩል አንቀጽ 114/3 የሠራተኛ ማህበራት በአንድ ላይ በመሆን የሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ሊመሰርቱ ይችላሉ በማለት ደንግጓል፡፡ በተጨማሪም የኢፌዲሪ አስፈጻሚ አካላት ተግባርና ስልጣን ለመወሰን የወጣዉ በአዋጅ ቁጥር 1263/2014 አንቀጽ 25/ ሰ/ሸ/ተ ሥር አሠሪዎችና ሠራተኞች በማህበር የመደራጀትና የኀብረት ድርድር የማድረግ መብቶቻቸውን እንዲጠቀሙ ያበረታታል፣ ይደግፋል፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚደራጁትን የሠራተኛና የአሠሪ ማህበራት ይመዘግባል፣
ማህበራትን ማጠናከር የሚያስገኘው ጠቀሜታ
• አሠሪና ሠራተኞች በጋራ ጥቅሞቻቸዉ ላይ በመመካከርና በመደራደር ስምምምነት ለመድረስ ይረዳል፣
• አሠሪና ሠራተኞች የሥራ ቦታቸዉን ምቹ ለማድረግ ይረዳል፣
• ዲሞክራሲያዊ ባህልን ብሎም መልካም አስተዳደርን በማዳበር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት እንዲመዘገብ አስተዋፆ ያደርጋል፤
• በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የሰመረ ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙት እንዲኖር እና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ሠራተኞች ግዴታቸዉን በአግባቡ እንዲወጡ ይረዳል፤
• ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ፣በሚገኘዉ ትርፍ የሠራተኛዉ ኑሮ እንዲሻሻል፣ እንቨስትመንት እንዲስፋፋና ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ያስችላል፤
• አሰሪና ሠራተኞችን ጥቅምና መብት በሚነኩ ጉዳዮች ላይ ሁለትዮሽና በሶስትዮሽ ማህበራዊ ምክከር ለማድረግ ያስችላል፤
• የሠራተኞች የሥራ ዋስትና እንዲረጋገጥ የደርጋል፡፡
የሠራተኞች በማህበር መደራጀት ምርትና ምርታማነትና ከማሳደግና የሠራተኞችንና የአሠሪዎችን መብት ከማረጋገጥ አንፃር ከላይ የተገለፁት ጠቀሜታዎች ያሉት በመሆኑ አሠሪዎች የሠራተኛ ማህበራትን በማቋቋምና በማጠናከር ረገድ ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

Read More Âť
News

ባለፉት ሦስት ዓመታት 9.8 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ባለፉት ሦስት ዓመታት 9.8 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
ባለፉት ሦስት ዓመታት 9.8 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች እውቀትን መሰረት ያደረገ ቋሚ የሥራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ባለፉት ሶስት ዓመታት መንግስት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማሳለጥ ብሎም የሀገሪቷን ልማት ለማፋጠን የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።
ብቁ የሰው ሀይልን በማፍራት ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ ፖሊሲዎች፣ አዋጅ እና የአሰራር ስርዓቶችን በመዘርጋት ተግባራዊ ማድረጉን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩም በእነዚህ ዓመታት በክህሎት የዳበረ አምራች ዜጋን የመፍጠር እና የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።
እንደ ሀገር ዜጎችን ከክህሎት አኳያ ማብቃት እና የስራ እድል መፍጠር ብቻ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ተወዳዳሪነት የማያረጋግጥ በመሆኑ የአሰሪና ሰራተኛ ግኑኑኝነትን ሰላማዊ ማድረግ ላይም መሰራቱን ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ብቁ እና ሙያ ያለው ዜጋን ለማፍራት የዘርፉን አሰራርና ተቋማቶችን የስልጠና አሰጣጥ ስርዓቶችን ማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።
ለላፉት ሶስት ዓመታትም አጫጭር የክህሎት ልማት ተግባራት ተጠናክረው የቀጠሉበት መሆኑን ተናግረዋል።
በባለፉት ሶስት ዓመታት ዘጠኝ ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች አጫጭር ስልጠናዎች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት እንዲያልፉ መደረጉን አብራርተዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት 9 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች እውቀትን መሰረት ያደረገ ዘላቂ የስራ እድል መፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የገበያ መረጃ ስርዓት ቴክኖሎጂ ዘርፉን ሙሉ በሙሉ በማዘመን የመረጃውን ተአማኒነት እንደሚያሳድገው አክለዋል።
ኢትዮጵያዊያን የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን ስራ ጠባቂ ከመሆን ይልቅ ስራን በራስ መፍጠር የሚያስችላቸውን አቅም ሊያጎለብቱ እንደሚገባ መግለፃቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል፡፡

Read More Âť
News

ኢንስቲትዩቱ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት የቴክኒክና ሙያ ማዕከል (UNEVOC) አባል ሆነ

ኢንስቲትዩቱ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት የቴክኒክና ሙያ ማዕከል (UNEVOC) አባል ሆነ፡፡
በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት የቴክኒክና ሙያ ማዕከል (UNEVOC) የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩትን አባል አድርጎ መቀበሉን አስታወቀ።
ማዕከሉ አባል ሀገራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓታቸውን እንዲያጠናክሩ ከመደገፍ ባለፈ የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች መፍጠር፣ የፈጠራ ፕሮጀክቶች መደገፍ፣ የአለም አቀፍ የእውቀትና ክህሎት ሽግግር እንዲሁም ትስስር እንዲፈጥሩ ዕድሎችን ይፈጥራል፡፡

Read More Âť
News

ተስፋ ሰጪው የወጣቶች የተቀናጀ ልማት …

ተስፋ ሰጪው የወጣቶች የተቀናጀ ልማት …
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተሰጠው ተልዕኮ አንዱና ዋነኛው የማክሮ ኢኮኖሚው ትልቁ ፈተና የሆነውን የሥራ አጥነት ምጣኔን በዘላቂነት መቀነስ ነው፡፡
በዚህም ፈጠራና ፍጥነት የታከለባቸው ሥራዎችን በየደረጃው ተግባረዊ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን ተጨባጭና ተስፋ ሰጪ ውጤቶችም መታየት ጀምረዋል፡፡
ከእነዚህ ሥራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የወጣቶች የተቀናጀ ልማት መርሃ ግብር ተጠቃሽ ነው፡፡
በዘርፉ የአምስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ላይ የኦሮሚያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ካሳ እንደገለጹት፤ የክልሉ መንግስት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው በሰጠው ትኩረትና ተግባዊ እየተደረገ ባለው የወጣቶች የተቀናጀ ልማት ፕሮግራም ተጨባጭ ውጤት ተገኝቶበታል፡፡
በክላስተር ደረጃ ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘው በዚህ ፕሮግራም ከ3ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ከመቶ ሺህ በላይ ወጣቶችንም የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለም አመላክተዋል፡፡
በክልሉ እየተተገበረ የሚገኘው የወጣቶች የተቀናጀ ልማት ሥራ በስንዴ ልማት፣ በጎጆ ኢንዱስተሪ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮ እርባታ፣ በቅመማ ቅመም፣ በአሳ እርባታ፣ በከብት ማድለብና መሰል ክላስተሮች ተለይተው እንደሆነ ያመላከቱት ምክትል ኃላፊው የክልሉ መንግስት የተለያዩ መንግስታዊ ድጋፎች እያደረገ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
en_USEN
Scroll to Top