bini


ከአብሮ ማደግ እስከ አብሮ መበልፀግ …
ከአብሮ ማደግ እስከ አብሮ መበልፀግ …
መገኛው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማረቆ ልዩ ወረዳ ሆቤ በሚባል ቀበሌ ነው፤ አብሮ አደግ ኢንተርፕራይዝ፡፡
በአካባቢው በመስኖ ሥራ በተሰማሩ አልሚዎች ተቀጥረው ይሰሩ በነበሩ አብሮ አደግ ወጣቶች በገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ በተደራጁ ወጣቶች የተመሰረተ ነው፡፡
ወጣቶቹ የርስ በርስ መስተጋብራቸው ይበልጥ ለማጎልበት አብሮ አደግነታቸውን ወደ ብልጽግና ለመቀየር አዋጭነቱን ተነግሯቸው ሳይሆን በተግባር አልፈውበት ባረጋገጡት የመስኖ ስራ ተሰማሩ፡፡
ተቀጥረው በሚሰሩበት ወቅት ያጠራቀሙት አስር ሺህ ብር ቆጥበው አንድ መቶ ሺህ ብር ተበድረው ወደ መስኖ ስራ የገቡት እነዚህ ወጣቶች በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የጓሮ አትክልቶችን ማምረት ጀመሩ፡፡
በገበያ ተፈላጊ የሆነ ምርት፣ በተሰማሩበት ሥራ የነበራቸው ክህሎት እና በሥራው የመቀየር ፍላጎታቸው ተዳምረው ወደ ውጤት ለመሸጋገር ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡
ወደ ሥራው ከተሰማሩበት ዕለት አንስቶ መንግስታዊ ድጋፍ ያልተለያቸው እነዚህ ወጣቶች አሁን ላይ ተቀጥሮ ከመስራት ወደ ቀጥሮ ማሰራት ተሸጋግረዋል፡፡ በዚህም 20 ለሚሆኑ ሥራ የሌላቸው ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል እና 200 ለሚሆኑት ደግሞ ጊዚያዊ የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል፡፡
በ8 ሄክታር መሬት ላይ በስፋት የመስኖ ሥራቸውን በማከናወን ላይ የሚገኙት እነዚህ ወጣቶች በአሁን ወቅት አጠቃላይ ሀብታቸው 12 ሚሊየን ብር ተሻግሯል፡፡ በልማት ያስተሳሰሩት አብሮ አደግነታቸው ወደ ብልጽግና እያሸጋገራቸው መሆኑን የተመዘገበው ውጤት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡
የኢንተርፕራይዙ ሰብሳቢ አቶ ሞሳ አብራር፤ ወጣቶች በዙሪያቸው ያለውን ጸጋ ቢመለከቱ እና ተደራጅተው ወደ ስራ ቢገቡ መቀየር እንደሚችሉ እኛ አይነተኛ ማሳያ ነን ይላል፡፡ በሥራ ሂደት ውስጥ በተለያዩ ጊዚያቶች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ቢያጋጥማቸውም ውጤት ከማስመዘገብ እንዳላስቆማቸውም ይናገራል፡፡
የአብሮ አደግ ኢንተርፕራይዝ ተግባራዊ የሥራ እንቅስቀሴ እና ለውጥ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የጀመረውን ቤተሰብ እና ማህበረሰብ የምርታማነት ማዕከል የማድረግ አዲሱ እሳቤን ማዕክል ያደረገ ነው፡፡


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!


በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
ያለንን ስትራቴጂያዊ አጋርነት ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት በውይይታቸው ላይ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት አኳያ እያከናወናቸው ያሉ የሪፎርም ሥራዎችንና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫችንን ከማየት ባለፈም ረዥም ጊዜ ባስቆጠረው የሁለትዮሽ ግንኙነት እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንም ተመልክተናል ብለዋል ፡፡
በቀጣይም የኢንተርፕሪነርሺፕ ስነ-ምህዳሩን ምቹ በማድረግ በተለይ የሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚያስችሉ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራትን ጨምሮ በቀጣይ በሚለዩ የትብብር መስኮች ላይ በጋር ለመሥራት ተግባብተናል፡፡
በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ የተጀመሩ ሥራዎችን በማጠናከርና በማስፋት የሁለትዮሽ ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ላሳዩት ቁርጠኝነትም አመስግነዋል፡፡


የአፍሪካ ልማት ባንክ ልዑካን ቡድን ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
በአፍሪካ ልማት ባንክ የግሉ ዘርፍ፣ መሠረተ ልማትና ኢንዱስትሪያላይዜሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሰለሞን ኩይኖር ከተመራው የአፍሪካ ልማት ባንክ ልዑካን ቡድን ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ለዜጎች ሰፊና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር በኢትዮጵያና በአፍሪካ የልማት ፈንድ መካከል በተፈረመው ስምምነት መሰረት የተከናወኑ ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ መመልከታቸውንና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችንም ማስቀመጣቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል፡፡
በአፍሪካ ልማት ባንክ የግሉ ዘርፍ፣ መሠረተ ልማትና ኢንዱስትሪያላይዜሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሰለሞን ኩይኖር እና የልዑካን ቡድን አባላት ለስምምነቱ ተግባራዊነት እያደረጉ ላለው ጠንካራ ድጋፍና ክትትልም አመስግነዋል፡፡


በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግስት መካከል የተፈረመውን ስምምነት ወደ ትግበራ ማስገባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጣሊያን መንግስት ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግስት መካከል የተፈረመውን ስምምነት ወደ ትግበራ ማስገባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጣሊያን መንግስት ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ የክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የክህሎት መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የተፈረመው ስምምነት በፍጥነት ወደ ትግበራ የሚሸጋገርበትን ሁኔታ በዝርዝር መመልከታቸውንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ስለማስቀመጣቸው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል ፡፡
በቅርቡ የተፈረመው ይህ ስምምነት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፉ በርካታ ሴቶችንና ወጣቶችን የሙያ ባለቤት በማድረግ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር በአፍሪካ በአይነቱ ልዩ የሆነውን የክህሎት ፓርክ በመገንባት ኢትዮጵያ ለያዘችው ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ጉዞ አይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
የጣሊያን ኤምባሲ ምክትል ልዕክ ኃላፊ ክቡር ሉካ ካርፒንቲየሪ፣ የጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ሚሼል ሞራና እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ስምምነቱን ወደ ተግባር እንዲሸጋገር እያደረጉ ላለው ያለሰለሰ ጥረትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡


ሥራው ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ፀጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው፡፡ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
ሥራው ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ፀጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው፡፡
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ውስጥ ከሚካተቱ አገልግሎቶች መካከል የቨርቹዋል የኢንተርፕራይዝ ምስረታ አገልግሎት ይገኝበታል።
ይህ አገልግሎት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስርዓቱ ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ጸጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ሥራው ሀገራዊ የመረጃ ስርዓትን ዘመኑን በሚዋጅ አሰራር የሚያዘምን ከመሆኑም ባሻገር ኢንተርፕራይዞች በአካባቢ ሳይወሰኑ የገበያ ድጋፍ እንዲያገኙ፣ አካታች የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር እና ጸጋቸውን ማዕከል ያደረገ ስልጠና እንዲያገኙ የሚያስችል ሆኖ መበልፀጉን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም ጠንካራና ተወዳዳሪ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች ለማፍራት ዜጎችን በሥርዓቱ የመመዝገብ እና እንዲደራጁ የማድረግ ሥራ በልዩ ንቅናቄ እና በትኩረት እንዲከናወን አሳስበዋል፡፡


ቀጣናዊ ትስስር በክህሎት ልማት …
ቀጣናዊ ትስስር በክህሎት ልማት …
የክህሎት ልማት ሥትራቴጂና አቅጣጫችን ከሀገራዊ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና አቅጣጫዎች ጋር እንዲሰናሰል ተደርጎ የተቃኘ ነው፡፡
ከዚህ አንፃር ከሀገራዊው ባሻገር ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተቀራርቦ በመስራት ቀጣናዊ የሙያ ብቃት ማዕቀፍ ተዘጃቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል፡፡
በዚህም ዜጎች ተንቀሳቅሰው የመስራት ብቻ ሳይሆን የመሰልጠን መብታቸው እንዲከበር ለማድረግ ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፡፡
ይህ በመሆኑም የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ በሀገራችን በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለቀጣናው ሀገራት ዜጎች የስልጠና ዕድል በመስጠት ብዙዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም ሰሞኑን በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ የሶማሊ ላንድ ዜጎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለጹት፤ ቢሮው ከከተማው ባሻገር የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮትን በትምህርትና ስልጠናው መስክ የማዋሃድ ሥራን በልዩ ትኩረት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
በዚህም 45 የሚሆኑ የሶማሊ ላንድ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ለምረቃ ማብቃቱን ገልፀው በቀጣይም ሌሎች የቀጣናው ሀገራትን ዜጎች የሥልጠና ዕድል በመስጠት ቀጣናውን በትምህርትና ስልጠና የማስተሳሰር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሠለሃዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ቀጣናውን በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው ስልጠናቸውን አጠናቀው ለምረቃ የበቁተት የሶማሌ ላንድ ዜጎች የህዝቦች ወንድማማችነት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡
