Mols.gov.et

bini

News

ከአብሮ ማደግ እስከ አብሮ መበልፀግ …

ከአብሮ ማደግ እስከ አብሮ መበልፀግ …
መገኛው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማረቆ ልዩ ወረዳ ሆቤ በሚባል ቀበሌ ነው፤ አብሮ አደግ ኢንተርፕራይዝ፡፡
በአካባቢው በመስኖ ሥራ በተሰማሩ አልሚዎች ተቀጥረው ይሰሩ በነበሩ አብሮ አደግ ወጣቶች በገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ በተደራጁ ወጣቶች የተመሰረተ ነው፡፡
ወጣቶቹ የርስ በርስ መስተጋብራቸው ይበልጥ ለማጎልበት አብሮ አደግነታቸውን ወደ ብልጽግና ለመቀየር አዋጭነቱን ተነግሯቸው ሳይሆን በተግባር አልፈውበት ባረጋገጡት የመስኖ ስራ ተሰማሩ፡፡
ተቀጥረው በሚሰሩበት ወቅት ያጠራቀሙት አስር ሺህ ብር ቆጥበው አንድ መቶ ሺህ ብር ተበድረው ወደ መስኖ ስራ የገቡት እነዚህ ወጣቶች በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የጓሮ አትክልቶችን ማምረት ጀመሩ፡፡
በገበያ ተፈላጊ የሆነ ምርት፣ በተሰማሩበት ሥራ የነበራቸው ክህሎት እና በሥራው የመቀየር ፍላጎታቸው ተዳምረው ወደ ውጤት ለመሸጋገር ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡
ወደ ሥራው ከተሰማሩበት ዕለት አንስቶ መንግስታዊ ድጋፍ ያልተለያቸው እነዚህ ወጣቶች አሁን ላይ ተቀጥሮ ከመስራት ወደ ቀጥሮ ማሰራት ተሸጋግረዋል፡፡ በዚህም 20 ለሚሆኑ ሥራ የሌላቸው ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል እና 200 ለሚሆኑት ደግሞ ጊዚያዊ የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል፡፡
በ8 ሄክታር መሬት ላይ በስፋት የመስኖ ሥራቸውን በማከናወን ላይ የሚገኙት እነዚህ ወጣቶች በአሁን ወቅት አጠቃላይ ሀብታቸው 12 ሚሊየን ብር ተሻግሯል፡፡ በልማት ያስተሳሰሩት አብሮ አደግነታቸው ወደ ብልጽግና እያሸጋገራቸው መሆኑን የተመዘገበው ውጤት አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡
የኢንተርፕራይዙ ሰብሳቢ አቶ ሞሳ አብራር፤ ወጣቶች በዙሪያቸው ያለውን ጸጋ ቢመለከቱ እና ተደራጅተው ወደ ስራ ቢገቡ መቀየር እንደሚችሉ እኛ አይነተኛ ማሳያ ነን ይላል፡፡ በሥራ ሂደት ውስጥ በተለያዩ ጊዚያቶች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ቢያጋጥማቸውም ውጤት ከማስመዘገብ እንዳላስቆማቸውም ይናገራል፡፡
የአብሮ አደግ ኢንተርፕራይዝ ተግባራዊ የሥራ እንቅስቀሴ እና ለውጥ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የጀመረውን ቤተሰብ እና ማህበረሰብ የምርታማነት ማዕከል የማድረግ አዲሱ እሳቤን ማዕክል ያደረገ ነው፡፡

Read More »
News

በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡

ያለንን ስትራቴጂያዊ አጋርነት ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት በውይይታቸው ላይ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት አኳያ እያከናወናቸው ያሉ የሪፎርም ሥራዎችንና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫችንን ከማየት ባለፈም ረዥም ጊዜ ባስቆጠረው የሁለትዮሽ ግንኙነት እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንም ተመልክተናል ብለዋል ፡፡
በቀጣይም የኢንተርፕሪነርሺፕ ስነ-ምህዳሩን ምቹ በማድረግ በተለይ የሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚያስችሉ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራትን ጨምሮ በቀጣይ በሚለዩ የትብብር መስኮች ላይ በጋር ለመሥራት ተግባብተናል፡፡
በኢትዮጵያ የሲውዲን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ የተጀመሩ ሥራዎችን በማጠናከርና በማስፋት የሁለትዮሽ ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ላሳዩት ቁርጠኝነትም አመስግነዋል፡፡

Read More »
News

የአፍሪካ ልማት ባንክ ልዑካን ቡድን ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡

በአፍሪካ ልማት ባንክ የግሉ ዘርፍ፣ መሠረተ ልማትና ኢንዱስትሪያላይዜሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሰለሞን ኩይኖር ከተመራው የአፍሪካ ልማት ባንክ ልዑካን ቡድን ጋር ውጤታማ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ ኢንተርፕራይዞችን በማጠናከር ለዜጎች ሰፊና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር በኢትዮጵያና በአፍሪካ የልማት ፈንድ መካከል በተፈረመው ስምምነት መሰረት የተከናወኑ ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ መመልከታቸውንና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችንም ማስቀመጣቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል፡፡
በአፍሪካ ልማት ባንክ የግሉ ዘርፍ፣ መሠረተ ልማትና ኢንዱስትሪያላይዜሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሰለሞን ኩይኖር እና የልዑካን ቡድን አባላት ለስምምነቱ ተግባራዊነት እያደረጉ ላለው ጠንካራ ድጋፍና ክትትልም አመስግነዋል፡፡

Read More »
News

በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግስት መካከል የተፈረመውን ስምምነት ወደ ትግበራ ማስገባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጣሊያን መንግስት ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡

በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግስት መካከል የተፈረመውን ስምምነት ወደ ትግበራ ማስገባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጣሊያን መንግስት ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ የክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የክህሎት መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የተፈረመው ስምምነት በፍጥነት ወደ ትግበራ የሚሸጋገርበትን ሁኔታ በዝርዝር መመልከታቸውንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ስለማስቀመጣቸው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል ፡፡
በቅርቡ የተፈረመው ይህ ስምምነት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፉ በርካታ ሴቶችንና ወጣቶችን የሙያ ባለቤት በማድረግ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር በአፍሪካ በአይነቱ ልዩ የሆነውን የክህሎት ፓርክ በመገንባት ኢትዮጵያ ለያዘችው ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ጉዞ አይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
የጣሊያን ኤምባሲ ምክትል ልዕክ ኃላፊ ክቡር ሉካ ካርፒንቲየሪ፣ የጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ሚሼል ሞራና እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ስምምነቱን ወደ ተግባር እንዲሸጋገር እያደረጉ ላለው ያለሰለሰ ጥረትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

Read More »
News

ሥራው ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ፀጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው፡፡ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ

ሥራው ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ፀጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው፡፡
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ውስጥ ከሚካተቱ አገልግሎቶች መካከል የቨርቹዋል የኢንተርፕራይዝ ምስረታ አገልግሎት ይገኝበታል።
ይህ አገልግሎት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስርዓቱ ዜጎች እምቅ አቅማቸውን ከአካባቢያዊ ጸጋ ጋር አሰናስለው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ሥራው ሀገራዊ የመረጃ ስርዓትን ዘመኑን በሚዋጅ አሰራር የሚያዘምን ከመሆኑም ባሻገር ኢንተርፕራይዞች በአካባቢ ሳይወሰኑ የገበያ ድጋፍ እንዲያገኙ፣ አካታች የብድርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር እና ጸጋቸውን ማዕከል ያደረገ ስልጠና እንዲያገኙ የሚያስችል ሆኖ መበልፀጉን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም ጠንካራና ተወዳዳሪ የሆኑ ኢንተርፕራይዞች ለማፍራት ዜጎችን በሥርዓቱ የመመዝገብ እና እንዲደራጁ የማድረግ ሥራ በልዩ ንቅናቄ እና በትኩረት እንዲከናወን አሳስበዋል፡፡

Read More »
News

ቀጣናዊ ትስስር በክህሎት ልማት …

ቀጣናዊ ትስስር በክህሎት ልማት …
የክህሎት ልማት ሥትራቴጂና አቅጣጫችን ከሀገራዊ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና አቅጣጫዎች ጋር እንዲሰናሰል ተደርጎ የተቃኘ ነው፡፡
ከዚህ አንፃር ከሀገራዊው ባሻገር ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተቀራርቦ በመስራት ቀጣናዊ የሙያ ብቃት ማዕቀፍ ተዘጃቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል፡፡
በዚህም ዜጎች ተንቀሳቅሰው የመስራት ብቻ ሳይሆን የመሰልጠን መብታቸው እንዲከበር ለማድረግ ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፡፡
ይህ በመሆኑም የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ በሀገራችን በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለቀጣናው ሀገራት ዜጎች የስልጠና ዕድል በመስጠት ብዙዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም ሰሞኑን በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ የሶማሊ ላንድ ዜጎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለጹት፤ ቢሮው ከከተማው ባሻገር የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮትን በትምህርትና ስልጠናው መስክ የማዋሃድ ሥራን በልዩ ትኩረት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
በዚህም 45 የሚሆኑ የሶማሊ ላንድ ዜጎችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ለምረቃ ማብቃቱን ገልፀው በቀጣይም ሌሎች የቀጣናው ሀገራትን ዜጎች የሥልጠና ዕድል በመስጠት ቀጣናውን በትምህርትና ስልጠና የማስተሳሰር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሠለሃዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ቀጣናውን በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው ስልጠናቸውን አጠናቀው ለምረቃ የበቁተት የሶማሌ ላንድ ዜጎች የህዝቦች ወንድማማችነት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡

Read More »
News

በሚኒስትሮች ምክር ቤት የጸደቀው የጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲ…

ፖሊሲውን ተከትለው እየተዘጋጁ የሚገኙት የህግ ማዕቀፎች ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ የተቃኙ ናቸወ፡፡
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የጸደቀው የጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲ እና ፖሊሲውን ተከትለው ተግባራዊ በሚደረጉ የህግ ማዕቀፎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡
በመድረክ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካን ጨምሮ የየክልሉ የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች እና የፌዴራል ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ተገኝተው መልዕት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት፤ በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት የጸደቀውን የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲ እና ፓሊሲውን ተከትለው እየተዘጋጁ የሚገኙት የህግ ማዕቀፎች ሚኒስቴሩ የጀመረውን የዘርፉ የለውጥ እሳቤ ላይ ያተኮሩ እና ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ማሳካት በሚያስችል መልኩ የተቃኙ ናቸው፡፡
የሥራ አጥነት ችግር መቅረፍ የሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ችግሮችን ለመቅረፍ እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው እነዚህ ፓሊሲዎች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች በዘርፉ የሚታዩ የአተገባበር ክፍተቶችን መቅረፍ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡
በመድረኩ አዲሱ የጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲ እና ፖሊሲውን ተከትሎ የሚወጡ የሕግ ማዕቀፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡

Read More »
News

ትምህርት ቤቱ እያንዳንዱ ተማሪ በመክሊቱ ስልጠና ማግኘት የሚችልበት ማዕከል ይሆናል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ትምህርት ቤቱ እያንዳንዱ ተማሪ በመክሊቱ ስልጠና ማግኘት የሚችልበት ማዕከል ይሆናል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል የሚሆን ‹‹የ21ኛው ክፍለዘመን ማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት›› ግንባታ አስጀመረ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ኢንስቲትዩቱ የሚያስገነባውን የ21ኛው ክፍለ-ዘመን ማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት ግንባታ በይፋ አስጀምረዋል፡፡
በማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ፣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች እና የኢንስቲትዩቱ አሰልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ግንባታውን ሲያስጀምሩ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ ትምህርት ቤቱ እያንዳንዱ ተማሪ በመክሊቱ ስልጠና ማግኘት የሚችልበት ማዕከል ይሆናል ብለዋል፡፡
በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፓሊሲ ላይ የተቀመጠውን የትምርት ስርዓቱን ቮኬሽናላይዝ የማድረግ ግብ ለማሳካት ከሚሰሩ ስራዎች አንዱ መሠል ተቋማትን መገንባት ይገኝበታል ብለዋል፡፡
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር በበኩላቸው የ21ኛው ክፍለ-ዘመን ማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት የክህሎት ማሳደጊያ ቦታ እንዲሆን ታስቦ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡
የመጀመሪያ ዙር ግንባታ የህጻናት መጫወቻን ጨምሮ በ1 ሺ 6 መቶ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚሰራ ሲሆን ከሁለት ወራት በኋላ ተጠናቆ ለስራ ዝግጁ እንደሚሆን ግንባታውን የጀመረው የግንባታ ተቋራጭ ገልጿል::

Read More »
News

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በተከናወኑ ስራዎች አዳዲስ ሀብቶች መፍጠር መቻሉን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በተከናወኑ ስራዎች አዳዲስ ሀብቶች መፍጠር መቻሉን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
የሥልጠና ተቋማቱ ዜጎች ሀብት የሚፈጥር የሥራ ሃሳብ አመንጪ እና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ አፍላቂ እንዲሆኑ እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል።
ክብርት ሚኒስትር ለኢዜአ እንዳሉት የክህሎት ልማት በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ዘላቂነትና ስራ አጥነት ቅነሳ አስፈላጊ እንደሆኑ ገልጸዋል።
ለክህሎት ልማት ደግሞ የስልጠና ተቋማትን የማመዘን፣ መሠረተ ልማት ማሟላትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ስራዎች ማከናወን ይጠይቃል ብለዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በተከናወኑ የለውጥ ስራዎች አዳዲስ ሀብቶች መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል።
በዚህም ተቋማቱ የሚያወጧቸውን ተማሪዎች ሀብት ፈጣሪ የሥራ ሃሳብ አመንጪና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ አፍላቂ እንዲሆኑ እያገዙ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የቴክኒክና የሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት በዚህ ቅኝት እንዲሰሩና ተደራሽነታቸው እንዲሰፋ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ውስጥ ዝንባሌና መክሊት ያላቸው ዜጎች በማዕከላቱ ሥራ መፍጠር እንዲችሉ እንደሚያደርግ ክብርት ሚኒስትር መግለፃቸው ጠቁሞ የዘገበው ኢኤአ ነው፡፡

Read More »
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
somSOM
Scroll to Top