Mols.gov.et

mols admin

News

#ለ2ኛ ዙር የሠመርካምፕ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልፀጊያ መርሃ ግብር ምዝገባ ተጀመረ።

#ለ2ኛ ዙር የሠመርካምፕ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልፀጊያ መርሃ ግብር ምዝገባ ተጀመረ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት እና የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢኒስቲትዩት ያዘጋጁት በአይነቱ ልዩ የሆነ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልጸጊያ መርሃ ግብር ወጣቶች የፈጠራ ሐሳባቸውን እና ችሎታቸውን ወደ ተጨባጭ ሥራ እንዲለውጡ በማስቻል ለአገራችን ሁለንተናዊ እድገት ትልቅ አበርክቶ ያላቸው ቴክኖሎጂዎች ማስገኘት የሚያስችል ነው።
በዚህ መርሃ ግብር ለሁለተኛ ዙር ምዝገባ ተጀምሯል። ስለሆነም በማንኛውም መስክ የቴክኖሎጂ እና የሥራ ፈጠራ ሐሳብ ያላችሁ በሙሉ ከነሐሴ 27/2016 ዓ/ም ጀምሮ ከታች ባለው ሊንክ ገብታችሁ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል።
https://forms.office.com/r/CNMFUUSZZe
#ማሳሰቢያ
📌 ምዝገባው የሚካሄደው በተቀመጠው ድህረገጽ ብቻ ነው
📌ከምዝገባ በኋላ በሚካሄድ ልየታ መሠረት ለሚመረጡ የፈጠራ ባለሙያዎች የሠመር ካምፕ ፕሮግራሙ የሚካሄደው አዲስ አበባ ላምበረት መነሀሪያ አካባቢ በሚገኘው የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋናው ካምፓስ ነው።

Read More Âť
News

በጀት ዓመቱ ሚኒስቴሩ የጀመራቸው ትላልቅ ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች ወደ ውጤት ተቀይረው ማየት የጀመርንበት ነው። ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ሥራና ክህሎት ሚኒስትር

በጀት ዓመቱ ሚኒስቴሩ የጀመራቸው ትላልቅ ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች ወደ ውጤት ተቀይረው ማየት የጀመርንበት ነው።
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
ሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የሚኒስቴሩ አመራሮች፣ የተጠሪ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልል እና ከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየገመገመ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል አፈጻጸሙን አስመልክተው ባቀረቡት ገለጻ፤ ሚኒስቴሩ በ2016 በጀት ዓመት በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና በአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ የተጀመሩ ትላልቅ ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች ወደ ተግባር ተሸጋግረው ውጤት ማስመዝገብ መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በክህሎት ልማት ዘርፍ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተኪ ምርት በማምረት የኩባንያ መፈልፈያ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች፣ ኢንተርኘሪነሪያል የሆኑ ተቋማት ለመገንባት የተሄደበት ርቀት፣ ተቋማቱ አካባቢያዊ ጸጋ መሠረት አድርገው እንዲለሙ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎች እንዲሁም ውጤታማ አጫጭር እና መደበኛ ስልጠናዎች ላይ የሚቆጠር ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል።
ከሥራና ሥራ ሥምሪት አኳያ ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ያረጋገጠ ጥራት ያለው የሥራ ሥምሪት በሀገር ውስጥም በውጭ ሀገር የተመዘገበበት በጀት ዓመት ነበር ብለዋል።
በተለይ በጀት ዓመቱ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ከመካከለኛ ምስራቅ ሀገራት በተጨማሪ መዳረሻ ሀገራት በማስፋት የሰለጠኑና በከፊል የሰለጠኑ ዜጎች በተዘረጋው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አማካኝነት ወደ አውሮፓ ሀገራት ለመላክ ስምምነቶች የተደረጉበት ወደ ሥራም የተገባበት መሆኑንም ተናግረዋል።
በአሠሪና ሰራተኛ ዘርፍም የኢንዱስትሪ ሰላም ለማረጋገጥ እና ምርታማነትን መሠረት ያደረጉ ጅምር ጥረቶች የተደረጉበት፣ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት እንዲሁም የመደራጀት ምጣኔ የመሣሰሉ ተግባራት ላይ አበረታች ስኬት መመዝገቡንም አብራርተዋል።
በበጀት ዓመቱ በየዘርፋ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ በዚህ መድረክ ለውይይት ቀርበው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ በቀጣይ የእቅድ አካል አድርጎ ለመፍታት ይሰራል ብለዋል።

Read More Âť
News

ስምምነቱ በግብርና ልማት ዘርፉ የተሰማሩና ተጨማሪ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እንተርፕራይዞችን የፋይናነስ አቅርቦት ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

ስምምነቱ በግብርና ልማት ዘርፉ የተሰማሩና ተጨማሪ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እንተርፕራይዞችን የፋይናነስ አቅርቦት ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ ሥራ ፈጣሪዎች ፋይናንስ ማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱ የተፈራረሙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ አያሌው(ዶ/ር) ናቸው፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በፊርማ ስነ-ስርዓት ወቅት እንደገለጹት፤ ግብርና በዘመናዊ መንገድ ለመስራት እየተደረገ ባለው ጥረት የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅሙ ማደጉን ገልጸው ይህ ስምምነትም በግብርና ልማት ዘርፍ የተሰማሩ እና ተጨማሪ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ ኢንተርፕራይዞችን የፋይናንስ ችግር መቅረፍ ላይ ትኩረቱ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለስራ ፈጣሪዎች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር እያደረገ የሚገኘውን ጥረት አድንቀው በግብርናው ዘርፍ የወጣቶችን አቅም ለመጠቀምና፣ እራስን ለመቻል እና አለፍ ሲልም ኤክስፖርት ለማድረግ እየተደረገ የሚገኘውን ጥረት የፋይናነስ አቅርቦቱ በእጅጉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡
የልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው ባንኩ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር የሚያቀርበው ይህ የፋይናንስ አቅርቦት የወጣቶች ኢንቨስትመንት ለማበረታታት እና በግብርና ሥራ ፈጠራ የተሰማሪ ኢንተርፕራይዞች የአዕምሮ ውጤታቸውን ያለምንም የፋይናንስ ተግዳሮት ወደ መሬት ማውረድ እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡
የፋይናንስ አቅርቦቱ ከተያዘው በጀት አመት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የተገለጸ ሲሆን ለአጠቃላይ ስራው 43 ሚሊዮን ዶላር ተመድቧል።

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በአጋርፋ

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በአጋርፋ እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶግራፍ

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በባህዳር

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በባህዳር እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶግራፍ

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በቴፒ

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በቴፒ እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶግራፍ

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በደሴ

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ #በደሴ እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶግራፍ

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በጎንደር

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ በጎንደር እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶ ግራፍ

Read More Âť
News

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” #በአርባ_ምንጭ

“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ በአርባ ምንጭ እየተሰጠ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና በፎቶግራፍ

Read More Âť
News

የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የመፃኢ ጊዜ እድላችንን ከሚወስኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር

የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የመፃኢ ጊዜ እድላችንን ከሚወስኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው፡፡
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ሃሳብ ከመላው ሀገሪቱ ለተወጣጡ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ አሁን ያለንበት ጊዜ እውቀት ብቻውን ምሉዕ እንደማያደርግ ከግምት በማስገባት ዓለም ላይ ለክህሎት ልማት ልዩ ትኩረት የተሰጠበት ወቅት ነው፡፡
እኛም እንደ ሀገር በዘርፉ መሰረት ለመጣል ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ በቅርቡ ለሀገራዊ ፍላጎቶቻችን ምላሽ የሚሰጥ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ይህም በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ይስተዋል ነበረውን ክፍተት የሚሞላ ብቻ ሳይሆን የሥልጠና ስርዓታችን ጊዜውን የዋጀና ለሀገራዊ ልማትና ብልጽግና ጉዞ የበኩሉን ድርሻ መወጣት የሚችሉ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያስችላል፡፡
ፖሊሲውን ተከትሎ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተግባራዊ ያደረገው አዲሱ የዘርፉ እሳቤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ልማት ፍላጎት የሚመልስ፣ በዘርፉ የነበሩ አለመጣጣሞችን የሚፈታ እንዲሁም አሰልጣኞችም ሆኑ ሠልጣኞች ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ይህም የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ እንደ ሀገር የመፃኢ ጊዜ እድላችንን ከሚወስኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ አሁን የሚሰጠው ስልጠና በዘርፉ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ አሰልጣኞች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማድረግ ባለፈ ባህሪያዊና ቴክኒካዊ ብቃቶችን በማሳደግ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት በ17 የስልጠና ማዕከላት የሚሰጠው ስልጠና በዘርፉ ልህቀትን ለማምጣት የሚያስችል እንደሆነ ያመላከቱት ክብርት ሚኒስትር በመድረኩ 24 ሺህ የሚጠጉ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል፡፡

Read More Âť
The Minister Is answering questions live in zoomClick To join the live Meeting
+
oroORO
Scroll to Top