የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው
የካቲት 10, 2026
የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ወደ ፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነት የሚያሸጋግረው የዘርፉ እሳቤ……
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከዚህ ቀደም የሚታወቁት በአጫጭር እና መደበኛ ፕሮግራም ያሰለጠኗቸውን ወጣቶች ሰርተፍኬት ሰጥተው በመሸኘት ነበር ፡፡ አሁን ግን ይህንን የተለመደ አሰራር የሚቀይር አዲስ እሳቤ ተቀርጾ በዘርፉ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል፡፡
እሳቤው ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸው ከሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ጋር የሚስማማ ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ የሚያስችል አዲስ እይታ ነው፡፡
በአሁን ወቀት ይህንን እሳቤ እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል፡፡ በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ 20% ቁጠባ እንዲቆጥቡ በማድረግ፣ ለሚመሰርቱት ኢንተርፕራይዝ መነሻ የሚሆን አቅም እንዲፈጥሩ እየተደረገ ይገኛል።
ከቴክኒካዊ ስልጠናው ጎን ለጎን በቀጣይ የኢንተርፕራይዝ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ስኬታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የኢንተርፕሪነርሺፕ እሳቤን ለመላበስ የሚያስችላቸውን ስልጠናም ከተቋማቱ ያገኛሉ፡፡
ኮሌጆች ያሏቸውን ማሽኖች ተጠቅመው እያመረቱ እንዲሰለጥኑ፣ እየሰለጠኑ እንዲያመርቱ የተቀመጠው አቅጣጫ ደግሞ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን ብቃትና ተወዳዳሪነት የሚያልቅ ሌላኛው የአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ገፅታ ነው፡፡
የቴክነኒክና ሙያ ተቋማት ጥራት ያለው ስልጠና አግኝተው፣ የኢንተርፕሪነርሺፕን ባህሪ ተላብሰው፣ በኮሌጆቹ ውስጥ በሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች እጃቸውን፣ ልባቸውንና አእምሯቸውን ቃኝተውና ኢንተርፕራይዝ መስርተው የሚወጡ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች የሚወጡባቸው ተቋማት ናቸው፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ዜጎች በስፋት የሚፈሩባቸው ማዕከላት እንዲሆኑ ማስቻል፣ የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ ስብራት የሚጠግኑ ባለወርቅ እጆች የሚፈጠሩባቸውና ሀገርን የሚያልቁ ኩባንያዎች የሚፈለፈሉባቸው የፈጠራና የጥበብ መናኻሪያነታቸውን ዕውን ማድረግ ደግሞ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተቀረፀው አዲሱ የክህሎት ልማት እሳቤ አዲሱ መዳረሻ ግብ ነው!







