መንግሥት ለጀመረው የሀገር በቀል ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ኢንተርፕራይዞች .
ሐምሌ 3, 2026
‹‹መንግሥት ለጀመረው የሀገር በቀል ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ኢንተርፕራይዞች የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንትና ዋና ሞተሮች ናቸው ››
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣ የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ፣ ሚኒስትር ዴኤታ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለዘርፉ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት በጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰሎሞን ሶካ፤ መንግሥት ለጀመረው የሀገር በቀል ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ኢንተርፕራይዞች የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንትና ዋና ሞተሮች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
ኢንተርፕራይዞች ይህን ወሳኝ ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የተቀረፀው የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲ የኢኮኖሚ ስብራቶችን ለመቅረፍ ፣ ዕድገትን ለማስቀጠልና ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቁልፍ ድርሻ እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በዘርፉ የነበሩ ድጋፎች የተበጣጠሱና አካታች ባለመሆናቸው ኢንተርፕራይዞች በአንድ ደረጃ ላይ ተንጠልጥለው እንዲቀሩ ማድረጋቸውን አስታውሰው፣ አዲሱ ፖሊሲ እነዚህን ማነቆዎች በዘላቂነት ለመፍታት የተዘጋጀ ሰነድ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢንተርፕራይዞች በሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ እድገት ላይ ዋንኛ ተዋናይ ወደሚሆኑበት ደረጃ እንዲሻገሩ የተፈጠረውን ምቹ የፖሊሲ አውድ በመጠቀም ለተግባራዊነቱ እያንዳንዱ የዘርፉ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ርብርብ እንዲያደርጉ ክቡር አቶ ሰለሞን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የአፍሪካ ልማት ባንክ የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ‹‹ በግብርና ኢንተርፕራይዞች ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮጀክት የፖሊሲውን ሰነድ በማሳተም፣ በማሰራጨትና የግንዛቤ መስጨበጫ መድረኩን በማዘጋጀት ላበረከተው የላቀ አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡





