ለአዳዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች የሳይኮሜትርክስ ምዘና …
የሳይኮሜትርክስ ምዘናው በባህር ዳር፣ በደብረታቦር እና በቦንጋ ፖሊ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጨምሮ በተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ተግባራዊ መደረጉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ምዘናው ለአዳዲስ ሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞች የሙያ መስክ ሲመርጡ በፍላጎቶት ብቻ ሳይሆን ተሰጥኦና ዝንባሌያቸውን መሰረት በማድረግ ውጤታማ ሊሆኑባቸው የሚችሉ የሙያ መስኮች እንዲመርጡ የሚያግዛቸው ነው።
የሥልጠና ጥራትና አግባብነት እንዲሁም ውጤታማነትን ከሥራ ገበያ ፍላጎቱ ጋር በማጣጣም ብቁ፣ በቂና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን በማፍራት እንደ ሀገር ለሥራ ገበያው ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ የቴክኒክና ሙያ ስርዓት ባለቤት እንድንሆን የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል ነው።