ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተወጣጡ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ፡፡
በጉብኝታቸው በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ እና ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኘውን የብየዳ ልህቀት ማዕከል እና በኢንስቲትዩቱ የተሰሩ ቴክኖሎጂዎችንና የሥራ እንቅስቃሴችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የሚዲያ ኃላፊዎቹም በጉብኝታቸው እና በተመለከቷቸው ሥራዎች መደሰታቸውንና በቀጣይ በጉዳዩ ላይ የባህሊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ሥራዎችን እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡