የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ተጠቀሚ መሆን ጀመሩ!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከ200ሺ በላይ ወጣቶች እና የመንግስት ስራተኞች ተመዝግበው ከ157ሺ በላይ ዜጎች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መውሰዳቸውን ተገለፀ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተጀመረው የ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች የዲጂታል ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩንም አብራርተዋል።
ሰልጣኞች የብቃት ማረጋገጫ ከማግኘት ባለፈ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማካኝነት የሥራ እድል ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውንም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂን ለማሳካት ሀገራችን የምታደርገው ጉዞ አካል ሲሆን በሦስት ኣመታት ውስጥ ሀገራችንን በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ ማድረግ የሚችሉ 5ሚሊዮን ሰዎችን ማብቃትን ዓላማው አድርጎ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡