የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ነው፡፡
በሩብ ዓመቱ በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራት በጥልቀት በሚገመገሙበት በዚህ መድረክ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሀመድ እና የዘርፉ አመራርና ሰራተኞች እየተሳተፉ ይገኛል።
በመድረኩ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ሥራዎች፣ የተገኙ ስኬቶችና ያጋጠሙ ችግሮችን በዝርዝር በመለየት የዘርፉን ዓመታዊ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ የቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡