Mols.gov.et

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ጋር ተወያዩ

October 1, 2024
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ጋር ተወያዩ በውይይቱ የሥራ ፈጠራ ስነ-ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ መንገስት እያደረገ ስላለው ጥረትና ሚኒስቴሩ እያከናወነ ስላለው ሥራ ክብርት ሚኒስትር ገለፃ አድርገዋል፡፡ በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን በመፍታትና ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የሥራ ፈጠራን ለማበረታታት ከሁሉም ባለድርሻ እና አጋር አካት ጋር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ክብርት ሚኒስትር ጠቁመዋል፡፡ ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ማህበሩ የጀመረውን ሥራ ያደነቁት ክብርት ሚኒስትር በቀጣይ ሚኒስቴሩ በሥራ ፈጠራው መስክ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከማህበሩ ጋር በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የማህበሩ መስራችና ፕሬዚዳንት ሳሚያ አብዱልቃድር የማህበሩን የቀጣይ ዓመታት ስትራቴጂክ ሰነድ (EYEA 2027) ለክብርት ሚኒስትር አስረክበዋል፡፡
oroORO
Scroll to Top