Mols.gov.et

ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት (World Skills) የሙሉ አባልነት ሰርተፊኬት ተቀበለች!

September 14, 2024
ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት (World Skills ) የሙሉ አባልነት ሰርተፊኬት ተቀበለች! የአለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት የኢትዮጵያን 88ተኛ የሙሉ አባልነት የማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ሰጥቷል። ኢትዮጵያ የአለምአቀፉ የክህሎት ድርጅት አባል መሆኗ በርካታ ፋይዳዎች ይኖሩታል። ከተለያዩ ሃገራት ጋር የኢንዱስትሪ ትስስር መፍጠር፣ በክህሎት ልማት ከተቀረው የአለም ክፍል ልምድ በመለዋወጥ እንዲሁም በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ልምዶችን በመቅሰም በዘርፉ እየተሠራ ባለው ሥራ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት እና ከተቀረው የአለም የክህሎት ልቀት ጋር እኩል ለመራመድ ሰፊ ምህዳር የሚፈጥር ይሆናል። አሁን እየተካሄደ በሚገኘው አለም የክህሎት ኦሎምፒክ ላይ ለመሳተፍ እና ከዓለም ጋር እርምጃችንን ለማስተካከል በእጅጉ የረዳን በመሆኑ ትልቅ የስኬት በር ከፋች እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ለዚህም ስኬት ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ! የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!
oroORO
Scroll to Top