Mols.gov.et

የሰለጠና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተጠቆመ

August 15, 2024
የሰለጠና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተጠቆመ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ሙክታር ከድር ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ በዘርፉ የተረደረገውን ሪፎርም ተከትሎ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ ሥምሪት ለማድረግ የተደረገው ጥረት በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት እንደነበር ተመላክቷል፡፡ በሳውዲ አረቢያ የሥራ ገበያ ከፍተኛ የሰው ሃይል ፍላጎት እንዳለና በዚህም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለመውሰድ በሚያስችል መልኩ በቅንጅት እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ በሳውዲ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት አኳያ የሰለጠና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡
en_USEN
Scroll to Top