የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ አፈጻጸምን ገመገመ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ አፈጻጸምን በጋራ ገምግሟል።
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳን ጨምሮ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ በሚኒስትር ዴኤታው ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የቀረበውን ሪፖርት መሠረት በማድረግ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የቀጣይ የትኪረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።