የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤት ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ በህጋዊ የውጭ አገር የሥራ ሥምሪት ዙሪያ ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ቺፍ ኦፍ ሚሺን አቢባቱ ዋኔ ጋር ተወወያዩ።
ክቡር አቶ ዳንኤል በውይይቱ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ህጋዊ የሥራ ስምሪቱን ማጠናከር ዋነኛው መፍትሄ በመሆኑ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የውጭ አገር የሥራ ስምሪትን አዋጅ አሻሸሎ ወደ ተግባር መግባቱን ገልፀዋል።
የዜጎችን መብት ደህንነት ለማስጠበቅ ከአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ቺፍ ኦፍ ሚሺን አቢባቱ ዋኔ በበኩላቸው በፍልሰት ለስራ ወደ ተለያዩ ሃገራት ለሚሄዱ ሰራተኞች መብትን የሚያሰጠብቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቀረጽ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሚሰራው ሥራ አሰፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደርጉ አረጋግጠዋል፡፡