የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳዮችን ከክርክር ይልቅ ወደ ምክክር ለመቀየር እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።
October 28, 2025
የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳዮችን ከክርክር ይልቅ ወደ ምክክር ለመቀየር እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።
የፌዴራል፣ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ የወሳኝ ቦርድ አባላት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአሠሪና ሠራተኞች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ወደ ክርክር ከመግባታቸው በፊት በስምምነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሥራዎች እየሠራ እንደሚገኝ በመድረኩ ተገልጿል።
በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ወሳኝ የሆኑ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸው እና መከለሳቸው የተገለፀ ሲሆን የአነስተኛ ደመዎዝ ቦርድ ደንብ እንዲዘጋጅ መደረጉ ፣ የአሠሪና ሰራተኛ ወሳኝ ቦርድ አሰራርና አደረጃጀት ሥነ ሥርአት ማንዋል እና የአሠሪ ሠራተኛ ቋሚ አማካሪ ቦርድ የቴክኒክ ኮሚቴ ጋይድላይን መዘጋጀቱም ተብራርቷል፡፡
በአፈጻፀም ሂደት ውስጥም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንደነበሩ በመድረኩ የተነሳ ሲሆን የወሳኝ ቦርድ እና አማካሪ ቦርድ የመስክ ክትትልና ድጋፍ የማጠናከር፣ የሥራ ክርክርን የሚቀንሱ ምርታማነትን የሚጨምሩ ሂደቱን በግብአት መደገፍና ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን የመከታተል ሥራዎች መሰራታቸውም ተብራርቷል፡፡
የፌደራል ወሳኝ ቦርድ የችሎት ስታንዳርድ እና የዲጂታል አሰራር ሂደትን ከባቢ የተሻለ ማድረግ በቀጣይ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የሚሰሩ ቁልፍ ተግባራት ሆነው ተቀምጠዋል።










