የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጅ አመራርና ሠራተኞች በኮሌጁ እና በኮሌጁ አካባቢ በሚገኙ አጎራባች ክልል ዞን እና ቀበሌዎች የአረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ የአካባቢን ስነ-ምህዳር ከሚጠብቁ ችግኞች በተጨማሪ ከ32 ሺህ በላይ የፍራፍሬ ችግኞችን መትከል መቻሉን የኮሌጁ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር መርክነህ መሰኔ ገልፀዋል፡፡
በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኮሌጁ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ባራ እና ናቃ ቀበሌዎች እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ ከ10 ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ የፓፓያ እና የሞሪንጋ ችግኝ መተከሉንም አመላክተዋል፡፡