የሥራ ሥምሪት አፈጻጸም
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የዘርፉን የመጀመሪያው እሩብ ዓመት አፈጻጸም ከክልል እና ከተማ አስተዳድር የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ገምግመዋል፡፡
የግምገማና ውይይት መርሃ ግብሩ አላማ በዋናነት በሩብ ዓመቱ የተቀመጡ ግቦች ከማሳካት አኳያ የተገኙ ስኬቶች ለማስፋት እና በጉድለት የታዩ አፈጻጸሞች በተያዘው እሩብ ዓመት እቅድ ተካተው እንዲተገበሩ ለማስቻል የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በግምገማ መድረኩ በዋናነት የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት አፈጻጸም ማላቅ፣ እሴት ሰንሰለትን የተከተለ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የሥራ ሥምሪት ማሳለጫ የሆኑት የሥራ ማዕከላት ሪፎርም እና ዘላቂ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩት የቤተሰብ እና የማህበረስብ ቢዝነስ ማስፋፋት ላይ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩና ከፍተኛ የማደግ አለኝታ ያላቸውን ኢንተርፕራይዞችን መደገፍ፣ በኢመደበኛ ንግድ የተሰማሩት ወደ መደበኛ ንግድ ዘርፍ እንዲገቡ ማድረግ እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች የገበያ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በድጅታል ስርዓት እንዲመዘገቡ ማድረግ ልዩ የአመራር ትኩረት የሚሹ የዘርፉ ተግባራት መሆናቸውንም ተገልጿል፡፡