የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ የካናዳ አምባሳደር ክቡር ጆሿ ታባህ ጋር ውጤታማ ውይይት አካሄዱ።
በውይይታቸውም ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ ያከናወነችውን ሪፎርም በዝርዝር ተመልክተዋል።
በዚህም ካናዳ ክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራን ጨምሮ በቀጣይ በሚለዩ መስኮች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠውልኛል ብለዋል ክብርት ሙፈሪሃት ፡፡
ኢትዮጵያ እና ካናዳ ከግማሽ ምዕተ ዓመት የተሻገረ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን በዘርፉ የሚደረገው ትብብርም ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው፡፡
በኢትዮጵያ የካናዳ አምባሳደር ክቡር ጆሿ ታባህ እና የሥራ ባልደረቦቻቸው በትብብር ለመስራት ላሳዩት ቀርጠኝነት ከብርት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ምስጋና አቅርበዋል፡፡