Mols.gov.et

በአቪየሽን እንዱስትሪው ያለንን ተወዳዳሪነት ለማላቅ…

January 13, 2024
የኢትዮጵ አየር መንገድ ሃገራችን በዓለም መድረክ ከፍ ብላ እንድትታይ ያስቻለ የስኬት ገፅ እና የመላው አፍሪካውያን ኩራት ነው። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬቶች ጋር አብሮ የሚነሳው የአቪየሽን ማሰልጠኛ በርካታ ባለሙያዎችን በማፍራት ሃገራችን በአቪየሽን እንዱስትሪው አንፀባራቂ ታሪክ እንድታስመዘግብ ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡ ብቁ የአቪየሽን ባለሙዎችን በማፍራት ይህንን የአገራችን የአቪየሽን እንዱስትሪ ስኬት ለማስቀጠል የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ፣የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል እና መንክር አቪየሽን ኮንሰልታንሲ ‹‹ኢሮ ክለብ›› በሚል ጥላ ሥር በመሰባሰብ በጋራ የፈረምነው የመግባቢያ ሰነድ አየር መንገዳችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የደረሰበትን ሥኬት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፤ ብቁ፣ በቂ እና ተወዳዳሪ ሙያተኞችን ለማፍራት ያለመ ነው። የኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል እና የመንክር አቪየሽን ኮንሰልታንሲ ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች በአቪየሽን እንዱስትሪው ያለንን ተወዳዳሪነታችንን ለማላቅ በትብብርና በቅንጅት ለመስራት ላሳያችሁት ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
en_USEN
Scroll to Top