Mols.gov.et

ለሴት ካውንስል አባላት የአመራርነት ሥልጠና ተሰጠ

March 30, 2024
ለሴት ካውንስል አባላት የአመራርነት ሥልጠና ተሰጠ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የሴቶች ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ የተዘጋጀና በዘመናዊና ውጤታማ የአመራር ስልቶች ላይ ያተኮረ ስልጠና ለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሴት አመራሮች ተሰጥቷል፡፡ በመድረኩ መክፈቻ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት የሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መከለያ ባርጊቾ፤ ስልጠናው ሴት አመራሮች ራሳቸውን ለማብቃትና እርስበርስ ልምድ ለመለዋወጥ በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዘርፈ ብዙ ተልዕኮዎችን የሚፈፅም ሚኒስቴር መ/ቤት እንደመሆኑ የሴት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት የሚሰሩ ሥራዎች አገራዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸው የገለፁት ወ/ሮ መከለያ መሰል መድረኮችን ማጠናከርና ውጤታማ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል፡፡ መሰል የአቅም ማጎልበቻ መድረኮች ያላቸውን ፋይዳ በመረዳት በቋሚነት ለማስቀጠል እንደሚሰራም የሴቶች ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እርቅነሽ ዮሃንስ ገልፀዋል፡፡
en_USEN
Scroll to Top