ፕሮጀክቱ በግብርና ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራን በማላቅ የሴቶችና ወጣቶችን
April 24, 2026
ፕሮጀክቱ በግብርና ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራን በማላቅ የሴቶችና ወጣቶችን ዘላቂ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ተገለጸ
የግብርና ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ለሥራ ፈጠራ (AMD4J) ፕሮጀክት ስትሪንግ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ የተገመገመ ሲሆን በተለይም የግብርና-ቴክኒክና ሙያ ሥልጠናን ማጠናከር፣ የሥራ ማዕከላት አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን እና የፋይናስ አቅርቦትና ተደራሽነትን ማሻሻል በሚቻልባቸው ጉዳች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በዚህም የወጣቶችንና የሴቶችን የኢኮኖሚ አቅም ከመገንባት አኳያ ያለው ሚና የላቀ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የግብርና ዘርፉንም ከማዘመን አኳያ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል።
በተጨማሪም በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ሥራ ፈጣሪዎችን የመቋቋም አቅም ማሳደግ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህም የኢንተርፕራይዞችን አደጋ የመቋቋም አቅም ማጎልበት ፕሮጀክት፤ በተለያየ ምክንያት ችግር የሚገጥማቸውን ኢንተርፕራይዞች መልሶ ለማቋቋምና ችግሮችን የመቋቋም ዝግጁነታቸውን በማሻሻል የዜጎችን ኑሮ በዘላቂነት ለመደገፍ የሚያስችል እንደሆነ የተመላከተ ሲሆን ስትሪንግ ኮሚቴው የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል፡፡








