Mols.gov.et

የአገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያው የአስተሳሰብና የባህሪ ለውጥ በሚያመጣ እና በተቀናጀ መልኩ መካሄድ እንዳለበት ተጠቆመ

August 15, 2024
የአገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያው የአስተሳሰብና የባህሪ ለውጥ በሚያመጣ እና በተቀናጀ መልኩ መካሄድ እንዳለበት ተጠቆመ የሥራና ክህሎት የአገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ ሥራዎች ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በተገኙበት ተገምግሟል፡፡ በመድረኩ የአገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ ሥራ የደረሰበት ደረጃ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በዚህም ሥራው በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡ ማሻሻያው የአስተሳሰብና የባህሪ ለውጥ በሚያመጣ እና በተቀናጀ መልኩ መካሄድ እንዳለበት የተጠቆመ ሲሆን የተጀመሩ ሥራዎችን ጥራት ባለው መልኩ በማስቀጠል ሁሉም ሠራተኛ በማሻሻው ላይ በቂ ግንዛቤ ገንዛቤ እንዲኖረውና ግብዓት እንዲሰጥበት እንደሚደረግም ነው የተገለፀው፡፡
tigTIG
Scroll to Top