
ፀጋን ማወቅ፣ ተጠቃሚነትን ማላቅ!
ፀጋን ማወቅ፣ ተጠቃሚነትን ማላቅ!
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ጋር በጀመርናቸው የትብብር ሥራዎችና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውጤታማ ውይይት አካሂደናል፡፡
የትብብር ትኩረታችን ያሉ ክልላዊ የልማት ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም በክህሎትና በሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
በቀጣይም የክልሉን የመልማት አቅም በሂደቱ የእውቀትና ክህሎት እንዲሁም ቴክኖሎጂ ሽግግር እውን ለማድረግና ሰፊና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል መፍጠር የሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ በዝርዝር መክረናል።
ይበልጥ አካታች፣ ዘላቂ፣ የኑሮ ዘዬው የተሻሻለና የበለፀገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሁሉን አቀፍ ጥረት ለማድረግም ተግባብተናል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አሻድሊ ሀሰን ቅንጅታዊ ሥራው እንዲሳካና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰጡት ላለው ጠንካራ አመራር ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረስዎ፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!