የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ክልል የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ ነው፡፡
በመድረኩ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘረፍ በግማሽ ዓመት አፈፃፀምና የሱፐርቪዥን ግኝቶች እንዲሁም በማህበራት ምጣኔ ማሳደግና አማካሪ ቦርድ ለማቋቋም በሚያስችለው የህግ ማዕቀፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመድረኩ በተቀመጠው የህግ ስርዓት መሰረት የአማካሪ ቦርድ እንዲቋቋምና ወደ ሥራ ለማስገባት እንዲቻል የአሠሪና ሠረተኛ ማኀበራት መደራጀት ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ ተነስቷል፡፡
በከልል የአሠሪና ሠራተኛ ማኀበር የመደራጀት ምጣኔ በማሻሻል የአማካሪ ቦርድ ለማቋቋም የአስፈፃሚ አካሉን አቅም ማጎልበትና በጉዳዩ ላይ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ መድረኩ መዘጋጀቱም ተጠቅሷል፡፡
የአሠሪዎችና ሠራተኞች በማህበር መደራጀት የኢንዱስትሪ ሰላምን ከማረጋገጥ ባሻገር ምርትና ምታማትን ለመጎለበት በሚኖረው ሚና እና በክልሎች የሚቋቋመው አማካሪ ቦርድ በሚኖረው ተግባርና ሃላፊነት ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡
በቀሪ ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችም ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡